Administrator

Administrator

በወጣት እና አንጋፋ ከያንያን እየቀረበ ያለው “ግጥም በጃዝ” 30ኛ ወርሐዊ ዝግጅት የፊታችን ረቡዕ እንደሚቀርብ አዘጋጆቹ አስታወቁ፡፡ ከቀኑ 11 ሰዓት ጀምሮ በራስ ሆቴል ትልቁ አዳራሽ በሚቀርበው ዝግጅት፤ አበባው መላኩ፣ ምንተስኖት ማሞ፣ ምስራቅ ተረፈ እና ዶ/ር በድሉ ዋቅጅራ ግጥም፣ ዲያቆን ዳንኤል ክብረት ወግ እንዲሁም መምህር እሸቱ አለማየሁ ዲስኩር የሚያቀርቡ ሲሆን የመግቢያ ዋጋው 50ብር ነው፡፡

ለአጭር ጊዜ ታምሞ ባለፈው ረቡዕ በተወለደ በ44 ዓመቱ ከዚህ ዓለም በሞት የተለየው አርቲስት ፈለቀ ጣሴ፤ከትላንት በስቲያ በደብረሊባኖስ ገዳም፣ ወዳጅ ዘመዶቹ በተገኙበት የቀብር ሥነሥርዓቱ ተፈፅሟል፡፡ በአዲስ ከተማ ት/ቤት ለመጀመርያ ጊዜ ከትያትር ጋር የተዋወቀው አርቲስት ፈለቀ፤ በኋላም የአርቲስት ተስፋዬ አበበ ትያትር ክበብን ተቀላቅሏል፡፡ አርቲስቱ በሀገር ፍቅር ትያትር - የጣር ሳቅ፣ የቀለጠው መንደር፣ ጥምዝ፣ የወፍ ጎጆ፣ ባልቻ አባ ነፍሶ እንዲሁም በአዲስ አበባ ትያትርና ባህል አዳራሽ - ቀስተ ደመና፣ የክፉ ቀን ደራሽ፣ የደም ቀለበት፣ ማዶ ለማዶ፣ ፍለጋ፣ ጣይቱ፣ ምርጫው፣ ሶስና እና የታፈኑ ጩኸቶች በተባሉ ትያትሮች ላይ ተውኗል፡፡ ሰርፕራይዝ እና ጥቁር ነጥብ በተሰኙ ፊልሞችም ላይ መስራቱ ይታወቃል፡፡

በደብረዘይት (ቢሾፍቱ) ከተማና አካባቢዋ የሥነጽሑፍ አፍቃሪያን የተቋቋመው “ሆራቡላ ሥነጽሑፍ ማሕበር” 20ኛ የስነጽሑፍ ዝግጅቱን የፊታችን ሰኞ ከቀኑ 7፡30 በከተማው ሕይወት ሲኒማ ትንሿ አዳራሽ እንደሚያቀርብ አስታወቀ፡፡ “የብዕር አዝመራ” በሚል ርእስ በሚቀርበው ዝግጅት፤ የማሕበሩ አባላት የግጥም፣ መነባንብ፣ ጭውውት እና ሌሎች ኪነጥበባዊ ሥራዎቻቸውን ያቀርባሉ፡፡ ከዚህም በተጨማሪ ዝነኛው የፊልም ተዋናይ ግሩም ኤርምያስ፤የህይወትና የሙያ ተመክሮውን ለማህበሩ አባላት እንደሚያካፍል ለማወቅ ተችሏል፡፡

በ1940ዎቹ የተመሠረተው ጐንደር ዩኒቨርስቲ የተመሰረተበትን የ60ኛ አመት የአልማዝ ኢዮቤልዩ በዓል ለአንድ ዓመት በተለያዩ ዝግጅቶች በማክበር ላይ ይገኛል፡፡ ዩኒቨርስቲው ዘንድሮ ከሚያስመርቃቸው ተማሪዎች በተጨማሪ በዓሉን ምክንያት በማድረግ 3ሺ የቀድሞ ተማሪዎችንም በድጋሚ ያስመርቃል ተብሏል፡፡ ዩኒቨርስቲው በማስገንባት ላይ ያለውን ሆስፒታልም በሰኔ ወር እንደሚያስመርቅ ታውቋል፡፡ በታህሳስ 25 ቀን 2000 ዓ.ም በይፋ የተከፈተው የዩኒቨርስቲው ክብረ በአል የተለያዩ ዝግጅቶች የቀረቡበት ሲሆን ክብረ በአሉ እስከ ሰኔ ወር መጨረሻ ድረስ ይዘልቃል ተብሏል፡፡ ዩኒቨርስቲው ባካሄደው የ6 ኪ.ሜ የሩጫ ውድድር ላይ ከ2000 በላይ የተሳተፉ ሲሆን የሆቴልና ቱሪዝም ተማሪዎች ለቡርባክስ ህዝቦች መታሰቢያ ያደረጉትን የአዝማሪ ቅኝት አቅርበዋል፡፡ ዩኒቨርስቲው ከመንግስት ጋር በመሆን በማስገንባት ላይ ያለው ባለ አንድ ሺ መኝታ ሪፈራል ሆስፒታል በሰኔ ወር እንደሚመረቅ ተነግሯል፡፡

The secret በተሰኘው የመጀመሪያ መጽሐፏ ከፍተኛ ዝናን የተቀዳጀችው አውስትራሊያዊ ደራሲ ርሆንዳ ባይርኔ The hero በሚል ያወጣችው ሦስተኛ መጽሐፏ “ጀግና” ተብሎ ወደ አማርኛ ተተረጐመ፡፡ መጽሐፉን የተረጐመው ብርሃኑ በላቸው ነው፡፡ “እያንዳንዳችን ወደዚህች ምድር የመጣነው በየራሳችን መንገድ ራሳችንንና ዓለምን የማበልጸግ ዓላማ ይዘን ነው” የሚለው መጽሐፉ፤ “አንተም ልዩ ነህና ለስኬት ተዘጋጅ” ይላል፡፡ 182 ገፆች ያሉት መጽሐፉ፤ በ40.50 እየተሸጠ ነው፡፡

በገጣሚ ሲሳይ ታደሰ /ዘ-ለገሐሬ/ የተፃፉ የግጥም ስብስቦችን የያዘው ‹‹ለፍቅራችሁ›› የተሰኘ የግጥም መድብል ሰሞኑን ለንባብ በቃ፡፡ 106 ግጥሞችን ያካተተው መድበሉ፤ “ለፍቅራችሁ” የሚል ርዕስ የተሰጠው መጽሐፉ ለህትመት እንዲበቃ ያገዙትን ሁሉ ለማመስገን እንደሆነ ገጣሚው ገልጿል፡፡ የግጥሙ መድበል ለአገር ውስጥ በ30 ብር፤ ለውጭ ደግሞ በ15 ዶላር ይሸጣል፡፡

በአስፋው መኮንን የተፃፈውና አስቂኝ፣ ቀልዶችና ቁምነገሮች የተካተቱበት መፅሀፍ ሰሞኑን ለንባብ በቅቷል፡፡ በአገራችን በቃል የሚነገሩ በርካታ አዝናኝና ቁም ነገር አስተማሪ ቀልዶች ቢኖሩም ብዙዎቹ በመፃህፍት ተፅፈው ስለማይቀመጡ የሚረሱና የሚደበዝዙ ይሆናሉ፤ ስለዚህም መመዝገብ አለባቸው ብሏል አዘጋጁ፡፡ በ158 ገፆች የተቀነበበው መፅሀፉ፤ በ35 ብር ለገበያ ቀርቧል፡፡

Saturday, 11 January 2014 12:11

“አለሁ ---- አልሞትኩም”

ረቡዕ ማታ በዛሚ 90.7 ኤፍ ኤም ሬዲዮ ላይ “አርቲስት ፈለቀ አበበ አረፈ” በሚል በስህተት በተነበበ ዜና እረፍት

ምክንያት አርቲስቱ፣ ቤተሰቦቹ፣ጓደኞቹና አድናቂዎቹ እስከ ሀሙስ እለት ተረብሸው ነበር፡፡ በርካቶች ዜናውን ባለማመን

ነገሩን ለማረጋገጥ አርቲስት ፈለቀ አበበ ተንቀሳቃሽ ስልክ ላይ ሲደውሉ ማምሸታቸውንና መዋላቸውን አርቲስቱ

ገልጿል፡፡ በስህተት ከተሰራጨው ዜና እረፍት በኋላ አርቲስት ፈለቀ የማር ውሃ አበበ ስለተፈጠረበት ስሜትና አጠቃላይ

ሁኔታ ከጋዜጠኛ ናፍቆት ዮሴፍ ጋር  አጭር ቃለምልልስ አድርጓል፡፡

የሞትህን ዜና በምን ሁኔታ ሰማህ?
ረቡዕ ወደ ማታ ቤት ቁጭ ብዬ እየሰራሁ ሳለሁ፣ ባልተለመደ መልኩ ስልኮች በተከታታይ መደወል ጀመሩ፡፡ አስደንጋጭ

ነበር፡፡ ብቻ የሆነ ነገር እንዳለ ያስታውቃል፡፡
ዜና እረፍትህን ሰምተው መደወላቸውን እንዴት አወቅህ?
አንዱን ጓደኛዬን በድፍረት ጠየቅሁት፡፡ ምክንያቱም በዚህ ፍጥነት በተከታታይ ሲደወል ለእኔ የተለመደ አይደለም፡፡

“ምንድን ነው ነገሩ? አካባቢው ላይ የተፈጠረ ነገር አለ እንዴ? ብዙ ሰው በተከታታይ እየደወለልኝ ነው” ብዬ

ስጠይቅ፤“አይ ሞተሀል ተብሎ በሬዲዮ ተነግሮ ነው” ሲለኝ ክው ብዬ ደነገጥኩኝ፡፡ ደግሞ ያስታውቃል፤ አንዳንዶቹ ልክ

ስልኬን አንስቼ “ሀሎ” ስላቸው ቶሎ ይዘጉታል። ብቻ መኖሬን ነው ማወቅ የሚፈልጉት፡፡ እንደዚህ ካደረጉት ውስጥ

ጓደኛዬ አርቲስት ሰለሞን ቦጋለ አንዱ ነው፡፡ አማኑኤል መሀሪ እንዲሁም ቤተሰቦቼም ድምፄን ሰምተው ብቻ ስልክ

ዘግተዋል፡፡ ምክንያቱም ወደ ቤተሰቦቼም ይደወል ነበር፡፡ ከውጭ አገር ሁሉ የስልክ ጋጋታው ሊያቆም አልቻለም፡፡
ሲደውሉልህ የሰዎች ስሜት እንዴት ነበር?
በጣም ህመም የሆነብኝ እሱ ነው፤ በጣም የሚያለቅሱና ኡኡ የሚሉ ነበሩ (ለቅሶ…) በጣም ያሳዝናሉ፤ እኔም አብሬያቸው

አለቅስ ነበር (ረጅም ለቅሶ)…
ሬዲዮ ጣቢያው ጋ አልደወልክም ?
ትንሽ ቆይቶ--- ከዛሚ 90.7 ኤፍ ኤም ደወሉልኝ፡፡ “በስህተት ነው ፈለቀ አበበ ሞተ ያልነው፤ የሞተው ግን አርቲስት

ፈለቀ ጣሴ ነው፤ አንተ በጣም ታዋቂ ስለሆንክ ፈለቀ ስንል አፋችን ላይ የገባው የአንተ አባት ስም ነው” አሉኝ፡፡ ነገር

ግን ሰው በጣም ያለቅሳል፤ በጣም ያሳዝናል፡፡
ይቅርታ ጠየቁ ወይስ----
እኔን በግሌ ይቅርታ ጠይቀውኛል፡፡ አድማጮችን ይቅርታ ይጠይቁ አይጠይቁ አላውቅሁም፡፡ ነገር ግን በነገሩ በጣም

አዝኛለሁ፡፡ ማንም ከሞት አይቀርም ግን እንዲህ ቀላል የሚመስሉ ስህተቶች ከባድ ጉዳት ያመጣሉ፡፡ ለምሳሌ በድንጋጤ

ልቡ ቀጥ የሚል ቤተሰብ፤ ወዳጅ ዘመድ ይኖራል፤ መሞት አለ --- ስንት ነገር አለ፡፡
በዚህ ድንገተኛ ክስተት ምን ተረዳህ?
እንዴ… በጣም በጣም ተገረምኩ እንጂ! ይህን ያህል ሰው ይወደኛል ወይ ነው ያልኩት፡፡ በጣም ደነቀኝ፡፡
ዜና እረፍትህ ከተነገረ ጀምሮ ምን ያህል ሰው ደውሎልሀል?
ከ500 በላይ ስልክ ተደውሏል፤ በግምት ወደ 600 ሳይጠጋ አይቀርም፡፡
ከዚህ በስህተት ከተሰራጨ ዜና እረፍት መልካም አጋጣሚ የምትለው ነገር አለ?
 እንደውም በጣም እድለኛ ነኝ አልኩኝ፡፡ በቁሜ ይህን ያህል ሰው እንደሚወደኝ ማየት ችያለሁ፡፡ ግርምቴ እስካሁን

አልቆመም፡፡
ከዚህ በፊት ያልሞተ ሰው ሞተ ተብሎ የተነገረበትን አጋጣሚ ታውቅ ነበር?
ሰምቼ አውቃለሁ፡፡ ነገር ግን ብዙዎቹን የሰማኋቸው ዛሬ (ሐሙስ ማለቱ ነው) ነው፡፡ ለምሳሌ ጥላሁን ጉግሳ የሚባል

ሌላ አርቲስት ሲሞት፣ በስም መመሳሰል በህይወት ያለው ጥላሁን የመሰለበት አጋጣሚ  ትዝ ይለኛል፡፡ ሌላ ጊዜ

በቴሌቪዥን አርቲስት ሲራክ ታደሰ ሲሞት፣ የአርቲስት አለሙ ገ/አብን ፎቶ ማሳየታቸው ትዝ ይለኛል፡፡ ያጋጥማል ነገር

ግን ሰው የሚያለቅሰው… መንገድ ላይ ሲያዩኝ የሚሆኑት ሁኔታ በጣም ያሳዝናል፡፡
አሁን እንዴት ነው ስልኩ ቀነሰ? አንተስ ተረጋጋህ?
ያው እየተረጋጋሁ ነው፡፡ አንድ ነገር ወደ አዕምሮዬ መጣ፡፡ የህይወት እስትንፋስን የሚሰጠው እግዚአብሔር ነው፡፡

የምንኖረውም እግዚአብሔር የፈቀደልንን ያህል ነው፡፡ ማናችንም ከተቆረጠልን ቀን አናልፍም፡፡ ግን እዛው ቤቴ ውስጥ

ቁጭ ብዬ፤ “አሁንስ ለመኖሬ ምን ማረጋገጫ አለ” ብዬ መፈላሰፍ ጀመርኩኝ፡፡ ከዚያ “ኦኬ በቃ አለሁ ማለት ነው…”

ማለት ጀመርኩኝ፡፡ አንዳንዶች እኮ “እርግጠኛ ነህ ፈለቀ ነህ የምታናግረኝ” ብለውኛል፡፡ ስለሞት ብዙ ነገር ነው

ያሰብኩት፡፡ ከምንወለድበት ቀን ይልቅ የሞት ቀን ይሻላል የሚለውንም አሰብኩኝ፡፡ እንደውም የአዲስ አድማስ ባለቤትና

መሥራች አሰፋ ጎሳዬ  ሲሞት አዲስ አድማስ ግቢ ሆኜ  የፃፍኩት ግጥም ነበር፡፡
ትዝ ይልሃል ---ምን የሚል ነው?
ቢርቅም አይጠፋም ይልቃል ከሽቶ
በሰው ልብ ይኖራል ከመቃብር ሸሽቶ፡፡   የሚል ነበር፡፡ አየሽ --- በዚህ አጋጣሚ ያየሁት የሰው ፍቅር፤ የበለጠ

የምሰራበትና መልካም ያልሆኑ ነገሮች ካሉኝም ለማሻሻልና ጥሩ ለማድረግ የምተጋበት ነገር ተፈጥሯል፡፡ የበለጠ መልካም

ሆኜ እንዳልፍ የሚያደርግ ጥሪም ነው፡፡ ደጋግሜ የምነግርሽ… ሰው ለእኔ የሆነው ነገር ገርሞኛል… እንዲህ ነው ወይ

የምትወዱኝ ነው ያልኩት፡፡
አንዳንዴ ሞት የሚያናድደው ከሞትክ በኋላ ሰው ለአንተ ያለውን ፍቅርም ሆነ ጥላቻ ማየት ባለመቻሉ  ነው አይደለ?
እውነት ነው፡፡ እህቴም እንደዚህ ነው ያለችው፡፡ እህቴ ምስጢር ደምሴ ስትነግረኝ፤ መንግስቱ የተባለ ደራሲ “ሞቻለሁ”

ብሎ ቀጨኔ መድሀኒዓለም ሰው ተሰብስቦ ዋይ ዋይ ሲል፣ እሱ ተደብቆ ማን ቀብር እንደመጣና እንዳልመጣ፣ ማን ከልቡ

እንዳዘነና እንዳላዘነ ይመለከት ነበር፡፡ ይሄ ይገርማል። እሱ አስቦበትና ተዘጋጅቶ ነው፡፡ እኔ ደግሞ ከዚህ በተቃራኒው

ሌሎች በፈጠሩት ስህተት፣ የህዝቡን ፍቅር አይቼበታለሁ፡፡ እኔ ልሳቀቅ፣ እኔ ልደንግጥላቸው (ለቅሶ…)
የሞትህ ዜና ሲነገር ስራ ላይ እንደነበርክ ነግረኸኛል፡፡ ምን እየሰራህ ነበር?
የመጽሐፍ ቅዱሱን ዮሐንስ ራዕይን በትረካ መልክ ለማቅረብ  እየተረጐምኩ ነበር፡፡ በመተርጐም ላይ ሳለሁ ነው ስልኩ

በተደጋጋሚ መደወል የጀመረው። ሀሙስ ጠዋት ከቤት ስወጣ ገርጂ አካባቢ “ዊሽ ስቱዲዮ” የሚባል ፎቶ ቤት አለ፤ ፎቶ

ሲያነሱኝ አየሁ፡፡
ለምን እንደሆነ አልጠየቅሃቸውም?
አልጠየቅኳቸውም፡፡ እነሱ ማታ ሞቷል መባሉን ሰምተው አድረው ኖሮ፣ ፎቶ ካነሱኝ በኋላ “Fele this morning”

ብለው ፌስ ቡክ ላይ ፖስት አድርገውኝ አየሁ፡፡ ሌላም ሰው “Still alive” ብሎ ፖስት አድርጓል --- እና የሚገርም

ነው፡፡
እና አሁን ምን ትላለህ?
አለሁ አልሞትኩም፤ ፈጣሪ እስከፈቀደልኝ እኖራለሁ፡፡ የሞተውን ወዳጃችንን ፈለቀ ጣሴንም ነፍሱን ይማርልን፡፡ ማርክ

ትዌይን  ያለውን እናስታውስና እንጨርስ፤ “ሞቴን በተመለከተ የወጣው ዘገባ ያለቅጥ  ተጋንኗል” እናም አልሞትኩም።

በዚህ አጋጣሚ አንዱ ጓደኛዬ መኪና እየነዳ “ፈለቀ አበበ ሞተ” ሲባል በድንጋጤ መኪናውን መቆጣጠር አቅቶት

ከመስመር ወጥቶ ሊጋጭ ለትንሽ ነው የተረፈው፡፡ እህቴም ቀድማ አልሰማችም እንጂ በልብ ድካም ትሞት ነበር፡፡

ስለዚህ ጋዜጠኝነት ትልቅና የተከበረ ሞያ በመሆኑ በጥንቃቄ ሊያዝና ሊከበር ይገባል እንጂ በቸልታ የሚሰራበት

አለመሆኑን ልገልጽ እወዳለሁ፡፡ የኢትዮጵያን ህዝብ እግዚአብሔር ያክብርልኝ፤ እኔም እወዳችኋለሁ፤ ስለተጨነቃችሁ

ስላዘናችሁልኝ አከብራችኋለሁ እላለሁ፤ አመሰግናለሁ፡፡  

Saturday, 11 January 2014 12:06

የቀን ብዙ

አድረን ልንገናኝ….
ነግቶ ልትመጪልኝ….
ለአንድ ቀን ባጣሁሽ፣
በዚሁ ቀን ብቻ - ብዙ ቀን ናፈኩሽ፡፡

ማዕድኑ ሰው
እግዜር አመዛዝኖ፣
ከአፈሩ ዘግኖ፣
መሬት ላይ በትኖ…
‹‹ሰው ሁን›› ካለው ወዲህ…
መኖር ያልደፈረ…
መሞት ያልጀመረ…
ለአንዱም ያልበቃ፣
በአንዱም ያልነቃ፣
ስንት አለ ጥሬ ዕቃ!?

የሴት ልጅ ነኝ
የሴት ልጅ መባሌ - ቂም አያስይዘኝም፣
ምክንያቱም አባቴ - አላረገዘኝም፡፡
        በገጣሚ ሲሳይታደሰ /ዘ-ለገሐሬ/

        ሶስተኛው መርህ የንግድ ተቋማት ለወጣት ሰራተኞች፣ ለወላጆች እንዲሁም ለተንከባካቢዎቻቸው ምቹ የሆነና አቅምን ያገናዘበ የስራ አከባቢን መፍጠር እንዳለባቸው ያትታል፡፡ ሰነዱ እንደሚያስረዳው ወጣት ሰራተኞች ስንል በህግ ለስራ ከተፈቀደው ዝቅተኛ የእድሜ ወሰን(14 አመት) የዘለሉና በገቢ ማስገኛ ስራዎች ላይ ተሰማርተው የሚገኙትን ነው ፡፡ የእነዚህ ወጣት ሰራተኞች ስራ ወይም የስራ ሁኔታ አደገኛ በሚሆንበት ጊዜም ከጉልበት ብዝበዛ ጋር ሊዛመድ የሚችልበት ሁኔታ አለ፡፡ መርሁ በተለይም ለነዚህ ወጣት ሰራተኞች የመስራት ፣ከአደጋ ነጻ የሆነ የስራ አከባቢ የማግኘት፣ጾታን ያማከሉ የውሃና የንጽህና መጠበቂያ አቅርቦቶችን ማግኘት ላይ አትኩሮት በመስጠት እንዲሰራ ግፊት ያደርጋል ስለዚህም የንግድ ተቋማቱ የእነዚህ ወጣት ሰራተኞች ጥቅም ከግምት በማስገባት ይህን ጉዳይ የሚያሥተዳድር መመሪያ እንደሚያስፈልጋቸው ያስረዳል፡፡በተጨማሪም የንግድ ተቋማቱ የወጣት ሰራተኞችን ጤና ማህበራዊ ደህንነት እንዲሁም ተከታታየይነት ያለው አቅም ግንባታን ያማከለ ምቹ የስራ ሄኔታና መፍጠር እንዳለባቸው ሃላፊነት ይሰጣል፡፡በተጨማሪም እነዚሁ ተቋማት ላረገዙ& ጡት ለሚያጠቡ እናቶች፣ለተንከባካቢዎች እንዲሁም ለስደተኛ ሰራተኞች ላይ ልዩ ትኩረት ማድረግ እንዳለባቸው ያስገነዝባል፡፡

አራተኛው መርህ የሚያተኩረው የንግድ ተቋማቱ በሚያከናዉኗቸው እንቅስቃሴዎች እና በአቅርቦታቸው የህጻናትን ደህንነትና ጥበቃን የማረጋገጥ ሃላፊነት እንዳለባቸው ያትታል፡፡ መርሁ የህጻናት እንዲሁም የወጣት ሰራተኞችን ጥቃትና ብዝበዛን ብሎም ደህንነታቸውን አደጋ ላይ ሊጥል የሚችል ማንኛውም የንግድ እንቅስቃሴ በመከላለክለና ፈጣን ምላሽ ለመስጠት የሚያስችል መመሪያ ማካተትን እንዲሁም አግባብነት ያለው እርምጃ ስለመውሰዳቸው የማረጋገጥ ሃላፊነት እንዳለባቸው ያስገነዝባል፡፡ በተጨማሪም መርሁ የንግድ ተቋማት የህጻናትን ደህንነትን አስመልክቶ በዘላቂነት ሊተዳደሩበት የሚገባ ፖሊሲ ሊኖራቸው እንደሚገባና በሰነዱ ላይም ቀጣይነት ያለው ስልጠና ከመስጠት ባሻገር ሊሎች ተመሳሳይ ተቋማትም ይህን መመሪያ እንዲያካትቱ ማበረታታትና ተነሳሽነትን መፍጠር እንዳለባቸው ያስረዳል፡፡ የንግድ ተቋማቱ የሚያመርቷቸው ምርቶችና የሚሰጧቸው አገልግሎቶች ከህጻናት ጥቅሞች ጋር የማይጻረሩ እንዲያውም ደጋፊ መሆናቸውን ማረጋገጥ የሚለው የአምስተኛው መርህ ዋነኛ መልእክት ነው ፡፡

በመርሁ መሰረትም ህጻናት ሊጠቀሙበት ብሎም ተጠቃሚ ሊሆኑ ይችላሉ ተብለው የሚታሰቡ ማንኛውም ምርቶችና አገልግሎቶች የአለም አቀፍ እና ሀገር አቀፍ ጥራታቸውን የጠበቁ ስለመሆናቸው፣ደህንነታቸው የተጠበቀ ስለመሆኑና ምንም አይነት የአካል፣የአእምሮና ሞራላዊ ጉዳት ላለማስከተላቸው ቅድሚያ መረጋገጥ እንዳለበት ይገልጻል፡፡በተጨማሪም የንግድ ተቋማቱ የሚያመርቷቸው ምርቶች ወይም የሚሰጧቸው አገልግሎቶች ለህጻናት ጥቃትና ብዝበዛ መሳሪያነት እንዳይውል ለመከላከል የራሳቸውን ጥረት የማድረግን ሃላፊነት ያስረዳል፡፡በዚህ መርህ መሰረት የንግድ ተቋማት ሃላፊነት የሚያጠነጥነው የምርትና አገልግሎታቸውን አቅርቦትና ስርጭት ተደራሽነት በማስፋት የህጻናት ጥቅሞች ማስጠበቅ ነው፡፡