ልብ-ወለድ
አባቴ ቀን ከሌት ነበር የሚፅፈው፡፡ በልጅነቴ ከጓደኞቼ ጋር ስጫወት ቆይቼ ቤት ስገባ ጠረጴዛና ወንበሩ መሀል አገኘዋለሁ፡፡ባለቅኔ ነው አባቴ፡፡ ቅኔው ግን ከሰዎች የመረዳት አቅም በላይ ስለሆነ ሰው ሳያውቀው፤ መጽሐፍ ሳይኖረው አለፈ፡፡ ፅፎ… ፅፎ… ፅፎ … ማሳተም ባይችል፤ አንድ ቀን ስራዎቹን ሰብስቦ…
Read 2687 times
Published in
ልብ-ወለድ
መኝታ ቤቴ ውስጥ ነኝ፡፡ መስኮቱ እንደተከፈተ ነው፡፡ ከውጪ የሚገባው ቀዝቃዛ ነፋስ አጥንት ድረስ ዘልቆ የሚሰማ ቅዝቃዜ ቢኖረውም፣ መስኮቱን ልዘጋው አልፈለግሁም:: ደረቴና ክንዴ እንደተራቆተ ነው፡፡ አብዝቼ በጠጣሁት መጠጥ ምክንያት የፈዘዙ ዐይኖቼን ከመኝታ አልጋዬ ፊት ለፊት ከቆመ የልብስ ቁምሳጥን ጋር አብሮ ከተሠራ…
Read 3079 times
Published in
ልብ-ወለድ
የመጽሐፌ ስኬት ፍርሃት ፈጠረብኝ የምትለው ደራሲ በዚህች አጭር ጽሑፌ የማወጋችሁ ኤልዛቤት ጊልበርት ከተባለች አሜሪካዊት ደራሲ የሰማሁትን ንግግር ነው፡፡ ከደራሲዋ ጋር ፊት ለፊት ተገናኝቶ የማውራት ዕድል አልገጠመኝም፡፡ በዲቪዲ የተቀረፀውን ንግግሯን የሰማና የተመለከተ ደራሲዋን አግኝቶ ለማውራት ቢቋምጥ ግን አትፍረዱበት፡፡ ንግግሯ ይጥማል፡፡ ሌክቸር…
Read 2737 times
Published in
ልብ-ወለድ
Saturday, 12 October 2019 12:22
አዳምና ቃየን
Written by ከመሐመድ ነስሩ (ሶፎንስያስ አቢስ) “ጥቁር ሽታ” የአጭር ልብወለድ መድበል የተወሰደ)
“ሔዋን…ሔዋን”እንደ እባብ ወደ ጐጆው ውስጥ እየተሳበ ይጣራል፡፡ ሀሳብ ጓዙን ጠቅልሎ፣ ግሳንግሱን በእጁ አንጠልጥሎ፤ ልቡ ውስጥ ውሎ ማደር ጀምሯል:: ሀሳቡ ምክንያት አልባ አልነበረም፡፡ ልጆቹ ከእናታቸው ጋር በፍቅር ሲተሻሹ አየ፡፡ ሚስቱ ልጆቿን እያገላበጠች ስትስም (ልክ እሱ መጀመሪያ እሷን ሲስማት እንደሆነው ልቧ ጥፍት…
Read 3262 times
Published in
ልብ-ወለድ
. . . እና ምን ይደረግ?ስለእናቶች ክብር እናት ያለው ሁሉ ተነስቶ ይውረግረግ?ሺ ሻማ ይለኮስ? ርችት ይተኮስ? አዲስ ጥበብ ቀሚስ ኩታ፣ ቅቤና አደስቀጤማ ይነስነስ? ምድሩ ይታረስ? በእንቁ ዕንቆጳዝዮን ልስራ እቴዋ መቅደስ?የት አባቴ ልድረስ አንቺን ለማወደስ?ውድ ሽቶ ይረጭ እጣን ጢሱ ይጨስ ከርቤና…
Read 3126 times
Published in
ልብ-ወለድ
ከስራ መጥቼ መክሰስ እንኳን ሳልበላ ወደ ጥናት ክፍል አመራሁ፡፡ የያዝኩትን ጥቁር ቦርሳ ከጠረጴዛ ላይ አሳረፍኩና መጋረጃውን ገልጬ መስኮቱን ከፈትኩት፡፡ ውጭ ህፃናት የእግር ኳስ ይጫወታሉ፡፡ ሌሎች ጥባጥቢ ያንጠባጥባሉ፡፡ ሌሎች ደግሞ አንድ ጅራፍ እየተቀያየሩ ያጮሃሉ፡፡መጋረጃውን ዘግቼ ጀርባዬን ለመስኮቱ ሰጥቼ፣ እጄን አጣምሬ ቆምኩኝ፡፡…
Read 3778 times
Published in
ልብ-ወለድ