Tuesday, 02 April 2024 09:48

የዓባይ ግድብ ግንባታ መታሰቢያ ቴምብር ይፋ ሆነ

Written by 
Rate this item
(1 Vote)
የኢትዮጵያ ፖስታ አገልግሎት የዓባይ ግድብ 13ኛ ዓመት ምክንያት በማድረግ ያዘጋጀዉን የመታሰቢያ ቴምብር በዓሉን በማስመልከት በተዘጋጀዉ የፓናል ዉይይት መድረክ ላይ ይፋ አደረገ።
የአባይ ግድብ የመታሰቢያ ቴምብሩን ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ተመስገን ጥሩነህ፣የዉሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ኢንጂነር ሀብታሙ ኢተፋ እና የአባይ ግድብ ማስተባበሪያ ጽህፈት ቤት ሀላፊ አረጋዊ በርሄ (ዶ/ር) በጋራ መርቀዋል።
የመታሰቢያ ቴምብሩ ከዛሬ ጀምሮ ለ192 የአለም አገራት እንደሚሠራጭ ተገልጿል።
Read 577 times