Saturday, 16 July 2016 12:12

ኢየሩሳሌም የህፃናትና ማህበረሰብ ልማት ድርጅት የመልካም ተሞክሮ ቀን አከበረ

Written by 
Rate this item
(8 votes)

    ኢየሩሳሌም የህፃናትና ማህበረሰብ ልማት ድርጅት፤ የማህበረሰብ ምስረታ ተቋማት የመልካም ተሞክሮ ቀን በዓል አከበረ፡፡ ድርጅቱ ሰሞኑን በቢሾፍቱ ከተማ ውስጥ በሚገኘውና የጄክዶ አፖርቹኒቲ ፎር ቼንጅ እየተባለ በሚጠራው የስልጠና ማዕከሉ ውስጥ ባከበረው በዚሁ የመልካም ተሞክሮ ቀን ክብረ በዓል ላይ የማህበረሰብ ምስርት ተቋማቱ ተወካዮች ተገኝተው ከድርጅቱ ጋር በማከናወን ላይ ስለሚገኙት የልማት ስራዎች ገለፃ አድርገዋል፡፡ “የማህበረሰብ ምስርት ተቋማት አጋርነት ለዘላቂ ልማት” በሚል መሪ ቃል በተከናወነው በዚህ የመልካም ተሞክሮ ቀን በዓል ላይ ተሞክሮአቸውን ለማካፈል ከተገኙት የማህበረሰብ ምስርት ተቋማት መካከል ዕድሮች፣ ማህበራትና የልማት ድርጅቶች ይገኙበታል፡፡ የእየሩሳሌም የህፃናትና ማህበረሰብ ልማት ድርጅት ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ሙሉጌታ ገብሩ በዚህ ወቅት እንደተናገሩት፤ ድርጅቱ በተለያዩ የአገሪቱ ክልሎች ውስጥ ከሚገኙ ከ140 በላይ የማህበረሰብ ምስርት ተቋማት ጋር በአጋርነት የሚሰራ ሲሆን በተለያዩ የልማት መስኮች በሺዎች የሚቆጠሩ ተጋላጭ የህብረተሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚ ያደረጉ ስኬታማ ስራዎችን አከናውኗል ብለዋል፡፡

Read 1584 times