Saturday, 11 June 2016 12:07

ህዳሴ ግድብ፤ በ5 ዓመት ወጪውን ሊመልስ ይችላል

Written by 
Rate this item
(17 votes)

• “በአመት 1 ቢ.ዶላር የውጭ ምንዛሬ ያስገኛል”
• ግድቡ የአፄ ኃይለስላሴ ህልም ነበረ - ታይም መጽሔት

ህዳሴ ግድብ ከአመት በኋላ ኤሌክትሪክ ማመንጨት እንደሚጀምር የዘገበው ታይም መጽሔት፣ ግንባታው፣ ከ4 ቢሊዮን ዶላር በላይ የሚፈጅ ቢሆንም፣ በየዓመቱ 1. ቢ ዶላር ገቢ ሊያስገኝ እንደሚችል ገለፀ፡፡
የአገሪቱ የኤሌክትሪክ አቅርቦት፣ የህዳሴ ግድብ ሲጨመርበት፣ አራት እጥፍ እንደሚሆን መጽሔቱ ጠቅሶ፤ የአገር ውስጥን የኤሌክትሪክ እጥረት ያቃልላል፤ ከሱዳንና ከግብጽ ማሰራጫ መስመሮች ጋር ሲገናኝም፣ በየዓመቱ 1 ቢ.ዶላር የውጭ ምንዛሬ እንደሚያስገኝ የኤምአይቲ ጥናት ያሳያል ብሏል፡፡
አፄ ኃይለስላሴ፣ ግድቡን የመገንባት ህልም እንደነበራቸውና የዛሬ ሃምሳ ዓመት ግንባታውን ለማካሄድ ወስነው እንደነበር አስታውሷል - መጽሔቱ፡፡ የገንዘብ እጥረት፤ የፖለቲካ አለመረጋጋት፣ ከባድ የድርቅ አደጋ፣ የደርግ መፈንቅለ መንግስት…ሌሎችም በርካታ ችግሮች ተደራርበው፣ የግድቡ ዕቅድ ለግማሽ ምዕተዓመት ዘግይቷል፡፡
በ2003 ዓ.ም በጠ/ሚ መለስ ዜናዊ ይፋ የተደረገው የግድብ ግንባታ፣ አሁን እንደተጋመሰና በግዙፍነቱ በአፍሪካ ቀዳሚ እንደሆነ መጽሔቱ ጠቅሶ፤ በግድቡ የሚፈጠረው ሃይቅ የወንዙን ውሃ ሙሉ ለሙሉ የማጠራቀም አቅም አለው ብሏል። በሚቀጥለው አመት ኤሌክትሪክ ማመንጨት እንደሚጀምርም መጽሔቱ በሰሞኑ እትሙ ገልጿል።

Read 10927 times