Sunday, 05 June 2016 00:00

እዝራ አብደላ - የጥበብ አድማስ !!!

Written by 
Rate this item
(18 votes)

      ሰው በሀገር ይወለዳል ይባላል። ግን ደግሞ ሀገርን የሚወልዱ ሰዎች አሉ።  
አብደላ እዝራ ጥበብና ፍቅር የተቃቀፉበት ሀገር በውስጡ ተሸክሟል።አብሮም ኖሯል።  የምናውቀው በተባ ብዕሩ፣በሰላ ሂሱ፣ስለ ጥበብ ሲል ሁሉንም በሚተው ኪናዊ ፍቅሩ ነው።  የአንጋፋ ደራስያንን ሥራ ፈትኗል፤የረገበውን የሀገር ጥበብ ቆንጠጥ አድርጎ በከፍታ አጉልቶ ለማሳየት።  ጠቢባን የሚያደንቁ ውብ ዓረፍተ ነገሮችን ዘክሯል። እምቡጥ አበቦቹን ወጣት ደራሲያንን በሚሳሳ እጁ ኮትኩቷል።  ቸርነቱ በጥበብም በቁስም ነው።   አብደላ እዝራ ጭው ባለ በረሃ ውስጥ ዕድሜውን ሙሉ ለጥበብ ንጽህና እንደ ምንጭ
የፈሰሰ ጅረት ነበር!   በፈረሰው  ቅጥር -----     የቆመ የጥበብ ዘብ!!
                                   *********   
        አንጋፋው የጥበብ ሃያሲና የአዲስ አድማስ ጸሐፊ እዝራ አብደላ፣ ቅዳሜ ግንቦት 28  ቀን 2008  ከዚህ ዓለም በሞት  ተለይቶናል። የቀብር ሥርዓቱ እሁድ ተፈጽሟል።  ለቤተሰቡ፣ለወዳጆቹ፣ለአድናቂዎቹና ለጥበብ አፍቃሪያን መጽናናትን እንመኛለን።


Read 5736 times Last modified on Tuesday, 07 June 2016 13:03