Saturday, 05 December 2015 08:46

“መሰረት በጎ አድራጎት”፤ በጉለሌ ያሰራውን የምንጭ ውሃ ማጎልበት ስራ ሰኞ ያስመርቃል

Written by 
Rate this item
(0 votes)

       ለችግር ተጋላጭ በሆኑ እናቶችና ህፃናት ላይ ትኩረት  አድርጎ የሚሰራው መሰረት በጎ አድራጎት ድርጅት፤ ጉለሌ ክ/ከተማ መቀጠያ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ 350 ሺህ ብር በማውጣት ምንጭ አገልብቶ የንፁህ መጠጥ ውሃ አጎልግሎት የሚያበረክተውን ፕሮጀክት፤ የፊታችን ሰኞ ረፋዱ ላይ ያስመርቃል፡፡ የጎለበተው ምንጭ ለአምስት ሺህ የአካባቢው ነዋሪዎች አገልግሎት እንደሚሰጥም የድርጅቱ መስራችና ዋና ዳይሬክተር ወ/ሮ መሰረት አዛገ ለአዲስ አድማስ ተናግረዋል፡፡ ፕሮጀክቱ በጉለሌ ክ/ከተማ ወረዳ 6 የደረቅ ቆሻሻ  አወጋገድ፣ የውሃ አቅርቦትና የንፅህና አጠባበቅ ፕሮጀክትን በሚደግፈው “ሲቪል ሶሳይቲ ስፖርት ፕሮግራም” ድጋፍ የተሰራ ሲሆን በተለይ በአካባቢው ባለው ከፍተኛ የውሃ እጥረት የሚንገላቱ እናቶችና ህፃናትን እፎይ ያሰኛል ብለዋል፤ ወ/ሮ መሰረት፡፡
የአካባቢው ህዝብ በጉልበት፣ በእውቀት በጥበቃ ስራና በቁፋሮ ከፍተኛ እገዛ ማድረጉን የጠቆሙት ዳይሬክተሯ፤ ይህ እገዛ ባይገኝ ኖሮ ፕሮጀክቱ 900 ሺህ ብር ይወስድ ነበር ብለዋል፡፡

Read 1495 times