Saturday, 10 October 2015 15:50

አምባሳደር ዘውዴ ረታ ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

 የታሪክ ፀሐፊ ጋዜጠኛና ዲፕሎማቱ አምባሳደር ዘውዴ ረታ ባለፈው ረቡዕ ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል፡፡ አምባሳደር ዘውዴ ረታ በተለይ “የኤርትራ ጉዳይ”፣ “የተፈሪ መኮንን ረጅም የስልጣን ጉዞ” እና “የቀዳማዊ ኃይለሥላሴ ዘመነ መንግሥት” የሚሉ የታሪክ መፅሃፍትን ፅፈዋል፡፡
በአዲስ አበባ ኦርማ ጋራዥ አካባቢ ነሐሴ 7 ቀን 1927 ዓ.ም የተወለዱት አምባሳደር ዘውዴ፤ እንግሊዝ ሎንደን ከተማ ዕረፍት ላይ እንዳሉ በድንገት በገጠማቸው ህመም ህይወታቸው ማለፉ ታውቋል፡፡አምባሳደር ዘውዴ በቀዳማዊ ኃይለሥላሴ ዘመነ መንግሥት በሬድዮ በቤተ መንግሥት ዜና አቅራቢነት የሰሩ ሲሆን፣ በቱኒዚያና በሌሎች ሀገሮች በአምባሳደርነትና በሌሎች የመንግሥት ኃላፊነቶች ላይም ሰርተዋል፡፡አምባሳደር ዘውዴ ረታ በቅርቡ በኤግዚቢሽን ማዕከል በተዘጋጀው “ንባብ ለህይወት” የመፅሃፍ አውደ ርዕይና ሸያጭ ላይ “የአመቱ የንባብ ለህይወት” የወርቅ ብዕር ተሸላሚ የነበሩ ሲሆን “የ2006 የበጐ ሰው” ተሸላሚም ነበሩ፡፡

Read 2711 times