Saturday, 19 September 2015 09:05

ልዩ የመስቀል ፕሮግራም ይካሄዳል

Written by 
Rate this item
(0 votes)

   አብርሃም ግዛው ኢንተርቴይመንትና ፕሬስ ስራዎች ድርጅት ከኢትዮጵያ ብሮድ ካስቲንግ ኮርፖሬሽን ጋር በመተባበር ልዩ የመስቀል በዓል ፕሮግራም ያካሂዳል፡፡ በኢቴቪ 3 ከቀኑ 11፡30 እስከ ምሽት 1፡30 ሰዓት ድረስ በሚተላለፈው በዚሁ ፕሮግራም ላይ የእርድ፣ የደመራ ማብራት፣ እና የአገር ሽማግሌዎች የምርቃት ስነስርዓት የሚካሄድ ሲሆን ባህላዊና ዘመናዊ ሙዚቃዎች፣ የኮሜዲ ዝግጅትና የመስቀል በዓል አከባበር ታሪካዊ ዳራ እንደሚቀርቡም ጋዜጠኛና ፕሮሞተር አብርሃም ግዛው ተናግሯል፡፡
በእለቱ ታዋቂ ሰዎች የኪነ ጥበብ ባለሙያዎች፣ የመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎችና ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ይታደማሉ ተብሏል፡፡ አብርሃም ግዛው ኢንተርቴይመንትና ፕሬስ ስራዎች ድርጅት “የጥበብ ብልጭታ” የተሰኘና በብስራት ኤፍኤም የሚተላለፍ የኪነ ጥበብ ፕሮግራም አዘጋጅ መሆኑ የሚታወስ ሲሆን የመስቀል በዓልን ዘንድሮ ለሁለተኛ ጊዜ ማዘጋጀቱም ታውቋል፡፡

Read 1374 times