Monday, 02 March 2015 08:43

6ቱ የአድዋ የእግር ተጓዦች ዛሬ እንደ አባ ገሪማ ይደርሳሉ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

119ኛውን የአድዋን የድል በዓል ለማክበር ጥር 15 ቀን 2007 ወደ አድዋ የእግር ጉዞ የጀመሩት ስድስቱ ተጓዦች ዛሬ “እንዳአባ ገሪማ” የሚባል ቦታ በሰላም መድረሳቸው ታውቋል፡፡
ሲሳይ ወንድሙ፤ መኮንን ሞገሴ፣ ጽዮን ወልዱ፣ ግደይ ስዩም፣ ታምሩ አሸናፊና አዳነ ከማል የተሰኙት እኒህ ተጓዣች እስካሁን በጉዟቸው ምንም ችግር እንዳልገጠማቸውና ሴቷም ተጓዥ ብትሆን በጉዞዋ ከወንዶቹ እኩል መቀጠል እንደቻለች ምንጮች ጠቅሰዋል፡፡ በነገው እለት አድዋ ገብተው የሶሎዳን ተራራ ግማሽ ያህሉን ወጥተው ያድራሉ የተባሉት ተጓዦቹ ሰኞ በማለዳ ተነስተው ወደ ሶሎዳ ተራራ ጫፍ በመውጣት ባንዲራ ከሰቀሉ በኋላ ተራራውን ወርደው አድዋ ከተማ ውስጥ የሚከበረውን የአድዋ 119ኛ በዓል እንደሚታደሙ ታውቋል፡፡ አምና 118ኛውን የአድዋ በዓል ለመታደም አምስት ተጓዦች ለ40 ቀናት በእግራቸው ተጉዘው አድዋ መድረሳቸው የሚታወስ ሲሆን የዘንድሮውን ጉዞ ሴት ተጓዥ መቀላቀሏ ለየት ያደርገዋል ተብሏል፡፡

Read 1897 times