Saturday, 10 January 2015 09:40

“ዳሽን አርት አዋርድ” ተዘጋጀ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

ዳሽን ቢራ ፋብሪካ በስነ ፅሁፍና በስዕል ጥበብ ላይ የተሰማሩ ደራሲያንን፣ ሰአሊያንንና  በዘርፉ እየሰለጠኑ የሚገኙ ልዩ ተሰጥኦ ያላቸውን ተማሪዎች የሚያሳትፍ በስነ ፅሁፍ፣ በግጥም እንዲሁም በስዕል ዘርፎች በማወዳደር በመሸለም በተሻለ ስራ እውቅና ሊያገኙ የሚችሉበትን መድረክ ማመቻቸቱን ገለፀ፡፡
በዚሁ በዳሽን አርት አዋርድ ላይ የሚሳተፉ ተወዳዳሪዎችን ለመዳኘት ከኢትዮጵያ ደራሲያን ማህበር፣ ከኢትዮጵያ ሰአሊያን ማህበር፣ ከዜማ ብዕር ኢትዮጵያ ሴቶች የስነፅሁፍ ማህበርና ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ስነ ጥበባት ተመርጠው መሄዳቸውም ተገልጿል፡፡
ዳሽን ቢራ ፋብሪካ አ/ማ ስፖርትና ኪነጥበብን በመሳሰሉ ሀገራዊ፣ ማህበራዊ እና ህዝባዊ የልማት እንቅስቃሴዎች ላይ ድጋፍ የሚያደርግ ድርጅት መሆኑ የሚታወቅ ነው፡፡

Read 1492 times