Saturday, 11 January 2014 10:32

ቀይ መስቀል ባለ 16 ፎቅ ህንፃ ሊያስገነባ ነው

Written by  ማህሌት ፋሲል
Rate this item
(1 Vote)

ከመንግስት 20 ሚ.ብር ይጠብቃል የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር በ5000ሚ. ብር ባለ 16 ፎቅ ህንፃ ሊያስገነባ እንደሆነ የገለፀ ሲሆን የህንፃ ማስገንቢያውን ገንዘብ “አንድ ብር ለሰብአዊነት” በሚል ዘመቻ ከህብረተሰቡ የሚሰበሰብ መሆኑን አስታውቋል፡፡ መንግስት በሦስት አመት ውስጥ 20ሚ. ብር ሊሰጣቸው ቃል እንደገባላቸው የገለፁት የማህበሩ ሃላፊዎች፤ ህብረተሰቡ ከአንድ ብር አንስቶ አቅሙ የፈቀደለትን በመለገስ ለህንፃው ግንባታ የበኩሉን አስተዋጽኦ እንዲያበረክት ጥሪ አቅርበዋል፡፡ በያዝነው ዓመት 127 ሚ.ብር ከህብረተሰቡ ለማሰባሰብ መታቀዱን የጠቆሙት የማህበሩ ሃላፊዎች፤ ህንፃው ተገንብቶ ሲጠናቀቅ በማከራየት ለማህበሩ የገቢ ምንጭነት እንደሚያገለግል አስታውቀዋል፡፡ ለማህበሩ የህንፃ ግንባታ ከ1 ብር ጀምሮ እርዳታ ለሚያደርግ ህጋዊ ደረሰኝ እንደሚሰጥም ታውቋል፡፡ በሰብዓዊ እርዳታና ድጋፎች ላይ የተሰማራው የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር፤ ከተቋቋመ 78 አመታትን ያስቆጠረ ሲሆን ወደ አምስት ሚሊዮን የሚጠጉ አባላት እንዳሉት ይታወቃል፡፡

Read 1622 times