Administrator

Administrator

በመጪው የኢትዮጵያ አዲስ ዓመት ዋዜማ ሸራተን አዲስ ሆቴል ታላቅ የሙዚቃ ድግስ አዘጋጅቷል። በዚህ ልዩ ምሽት በዓለም አቀፍ ደረጃ ታዋቂ የሆነው አሜሪካዊው ራፐር ቲ.አይ (T.I.) እና አንጋፋዋ የሙዚቃ ንግሥት አስቴር አወቀ በአንድ መድረክ ላይ ሥራዎቻቸውን ያቀርባሉ። ሆቴሉ "ጥበቃው አብቅቷል!" በማለት ባወጣው መግለጫ ሁለቱ ታዋቂ አርቲስቶች በዋዜማው እንደሚያቀነቅኑ አስተዋውቋል፡፡
የሂፕ-ሆፕ አውራው ቲ.አይ እና የሀገራችን የሙዚቃ ንግሥት አስቴር አወቀ የሚገናኙበት ይህ ድግስ፣ በአዲሱ ዓመት አቀባበል ከሚደረጉ ትልልቅ ዝግጅቶች ሁሉ ቀዳሚው እንደሚሆን ተጠቁሟል። ሁለቱ ድንቅ አርቲስቶች የሚያቀርቡበት ይህ ታሪካዊ ምሽት፣ አዲስ ዓመትን በታላቅ ድምቀትና ደስታ ለመቀበል የተዘጋጀ የማይረሳ መድረክ ነው ተብሏል።
የቴሌግራም ቻናልችንን በመቀላቀል የአዲስ አድማስን መረጃ ይከታተሉ…
የቴክሳስ ምሽት ዛሬ የተለየ ነው። ሰማዩ ሰፊ፤ ከዋክብቱ በሩቅ ጸጥ ብለው የማላውቀውን የትዝታ በር ከፈተብኝ። ሰውነቴ እዚህ ቴክሳስ፤ ሐሳቤ ግን ውቅያኖስ ተሻግሮ፣ ዓመታትን ወደኋላ ተጉዞ፣ አዲስ አበባ .... መርካቶ።
የመርካቶ ልጅ ነበርኩ። መርካቶን ኖሬበታለሁ፣ በመንገዶቹ ላይ አድጌበታለሁ። ገሊላ ትምህርት ቤት እየተማርኩ፣ ከዜድ ሙዚቃ ቤት እስከ ሸንኮራ ተራ፣ ከአብነት እስከ ኮካ ኮላ ያሉት መንገዶች የልጅነቴ ካርታ ነበሩ። ጩኸቱን አውቃለሁ፤ ሽታውን አውቃለሁ፤ የሱቆቹን ትርምስ፣ የነጋዴዎቹን ድርድር፣ የሻይ ቤቶቹን ወሬና የሰዎቹን ቀልድ አውቃለሁ። የመርካቶን ማለዳ በእግሬ አልፌበታለሁ፤ ምሽቱንም በድምፁ አውቀዋለሁ።
ለእኔ መርካቶ የአዲስ አበባ አንድ ሰፈር ብቻ አልነበረም፤ ልጅነቴ የተጻፈበት ቦታ፣ ዓለምን ማየት የጀመርኩበት መስኮት ነበር። መርካቶ ገበያ ብቻ አልነበረም፤ በጥቂት ካሬ ኪሎ ሜትሮች ውስጥ የተሰበሰበች ትንሽ ኢትዮጵያ ነበረች። ከጎንደር የመጣው፣ ከወሎ የወረደው፣ ከጎጃም የመጣው፣ ከሐረር፣ ከወለጋ፣ ከጉራጌ፣ ከትግራይ፣ ከአርሲና ከሲዳማ የመጡ ሰዎች በየመንገዱ፣ በየሱቁና በየሻይ ቤቱ ይገናኙ ነበር። የንግግር ዘዬያቸው ይለያይ ነበር፤ ምግባቸው፣ ልማዳቸውና እምነታቸውም ይለያይ ነበር፤ ግን መርካቶ ሁሉንም በአንድ ትልቅ ግቢ ውስጥ እንደሰበሰበች እናት ታቅፋቸው ነበር። ዛሬ ሳስበው
መርካቶ በልጅነቴ ያስተማረችኝ ትልቁ ትምህርት ይህ ይመስለኛል፤ ኢትዮጵያ በካርታ ላይ ብቻ አልነበረችም፣ በሰዎች ዕለታዊ ኑሮ ውስጥ ነበረች። ምናልባትም ያኔ ሳናውቀው የምንኖረው ነገር፣ ዛሬ በብዙ ቃላት የምንፈልገው ነገር ነበር፣ አብሮነት።
ልጅ ሆኜ እነዚያን ሰዎች ስመለከት ስለ “አብሮነት” ትልቅ ፍልስፍና አልገባኝም ነበር። አብሮነት ለእኛ ንግግር አልነበረም፤ የዕለት ተዕለት ኑሮ ነበር። የሙስሊሙን ሱቅ ክርስቲያኑ ይጠብቅለታል፤ የክርስቲያኑንም ችግር ሙስሊሙ ይጋራል። ከየአቅጣጫው የመጡ ሰዎች ከጠዋት እስከ ማታ በአንድ መንገድ ላይ ሕይወትን ይካፈሉ ነበር። ፍጹም ነበር ማለት አይደለም፤ ችግርም ጠብም ነበር። ግን ልዩነት ሁልጊዜ ግድግዳ አልነበረም።
ምናልባት ለዚህ ነው ዛሬ የቴክሳስን ሰፊ ሰማይ ስመለከት የሚናፍቀኝ ሕንፃዎቹ ወይም መንገዶቹ ብቻ ያልሆኑት። ሰዎች ናቸው የሚናፍቁኝ። ያ አንዱ ሌላውን የሚያውቅበት፣ በቀልድ የሚጠራራበት፣ ቡና የሚጋበዝበት፣ በችግር የሚደራረስበት የመርካቶ ሕይወት ....
ዓመታት አለፉ። ከተሞች ተቀየሩ፤ ሰዎች ተበተኑ፤ እኛም ዓለምን ተሻገርን። ግን ትዝታ ድንበር አያውቅም። ፓስፖርት አይጠይቅም፤ ቪዛም አያስፈልገውም። አንድ የሌሊት ንፋስ፣ አንድ የቡና ሽታ፣ አንድ የቆየ ዜማ በቂ ነው፤ በአንድ ቅጽበት ወደ ልጅነትህ ይመልስሃል።
ዛሬ ቴክሳስ ነኝ። ከፊቴ ሰፊው የቴክሳስ ሰማይ ተዘርግቷል። በዓይኔ ከዋክብቱን አያለሁ፤ በልቤ ግን የመርካቶን መንገዶች እጓዛለሁ። ዛሬ አዲስ አበባን “የእኔ ናት” ብለው በብቸኝነት የሚጠይቁ ሰዎች፤ እንዲህ ያለ ትዝታ ይኖራቸው ይሆን?
ዶ/ር መኮንን ብሩ
 
 

የቀድሞው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ስራ አስፈጻሚ የኡጋንዳ አየር መንገድ ስራ አስፈጻሚ ሆነዋል።
.
አቶ ግርማ ዋቄ ሊፈርስ የደረሰውን አየር መንገድ እንዲያቀኑ ነው ከፍተኛ ሀላፊነት የተጣለባቸው።
????????
ታዲያ ከሰሞኑ ለኡጋንዳ ፓርላማ ሪፖርት ሲያቀርቡ ነበር: ከፍተኛ ውዝግብ ያስነሳ ሪፖርት ነው ያቀረቡት። አቶ ግርማ አየር መንገዱ በሙስና የተነሳ መበስበሱን ገልፀዋል። ኡጋንዳ አየር መንገድ ካሉት 8 አውሮፕላኖች ውስጥ 2ቱ ብቻ እንደሚሰሩ አሳውቀው፤ አየር መንገዱ አደጋ ላይ መሆኑን አቀረቡ።

የኡጋንዳ ፓርላማ "መቼ ነው ከክስረት ወጥተን ማትረፍ የምንጀምረው?" ብሎ በጉጉት ሲጠይቅ አቶ ግርማ "እስከ 2033 ትርፍ የሚባል ነገር አይታሰብም፤ እቅጩን እወቁት" አሉ።
????????
ይህንን ስንሰማ በአመት 9.1 ቢሊየን ዶላር ገቢ ባስገኘው Ethiopian Airlines /የኢትዮጵያ አየር መንገድ እንኮራለን ስሙንም ከፍ በኩራት እናደርጋለን።

በአመታቶች ውስጥ የስራ አስፈጻሚዎቹ ስልታዊ አመራር፤ የሰፋተኞቹ ታታሪነት እና የመንግስታት ድጋፍ ባበረከቱት አስተዋጽኦ አየር መንገዳችን ከአለም አቀፍ ስመጥር አየር መንገዶች አንዱ ሆኗል።

ዌል እንግዲህ
ባለበት የሚፀና በርትቶ የቆየ ነውና አየር መንገዱ በብርታቱ እንዲቀጥል የሚስተዋሉ የመንገደኞች መጎሳቆል፤ የሻንጣ መጥፋት፤ የሰራተኞች በሙስና መጠመድ፤ የሚታወቅበት hospitality መቀነስ ሊሰራባቸው ይገባል።

Zemelak Endrias-

የቴሌግራም ቻናልችንን በመቀላቀል የአዲስ አድማስን መረጃ ይከታተሉ…
https://t.me/AdissAdmas

በደራሲ ንጉሥ ታደለ ድሪባ የተዘጋጀው እና 340 ገጾችን የያዘው “አዲሱ የዓለም ሥርዓት” (New World Order) የተሰኘ መጽሐፍ በቡራዩ ኩሪፍቱ ሪዞርት በይፋ ተመረቀ። መጽሐፉ ዓለም በአንድ የገንዘብ ሥርዓት፣ በአንድ ንጉሥ እና በአንድ የአመራር እዝ ስር ስትመራ የበለጠ ፍትሃዊነትና እኩልነት ይሰፍናል የሚል አከራካሪ እናለየት ያለ ሃሳብ ያነሳ ሲሆን፣ ደራሲው ለዚህ አዲስ ሥርዓት ራሳቸውን እንደ ዋነኛ እጩ አቅርበዋል።

በምረቃ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ የተገኙት የሀገራዊ ቤተ-መዛግብትና ቤተ-መጻሕፍት ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር አቶ ሰርፀፍሬ ስብሀት እና ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የመጡት ዶክተር ገዛኸኝ ፀጋው፣ መጽሐፉ የምርምር አስተሳሰብን ለማሳደግ እና በአለም አቀፍ ደረጃ ሊወያዩበት የሚችሉ አዳዲስ ሀሳቦችን ለማፍራት ትልቅ ሚና እንዳለው ገልጸዋል።

ይህ በአማርኛ፣ በኦሮምኛ እና በእንግሊዝኛ ተዘጋጅቶ ከሀገር አልፎ ለዓለም አቀፍ አንባቢያን እንዲደርስ ወደ 13 ተጨማሪ ቋንቋዎች የተተረጎመው መጽሐፍ የምረቃ መርሐ-ግብር ታዋቂ አርቲስቶች፣ ምሁራን እና የፈጠራ ባለሙያዎች በተገኙበት በድምቀት ተካሂዷል።

የቴሌግራም ቻናልችንን በመቀላቀል የአዲስ አድማስን መረጃ ይከታተሉ…
https://t.me/AdissAdmas

የኦርቶዶክስ እምነት ሥነ-መለኮታዊ፣ ምስጢራዊና ማኅበራዊ ትውፊቶች ለዘመናዊው ዓለማዊ እና ውስብስብ የአመራር ንድፈ-ሐሳብ ያበረከቱት አስተዋጽኦ እጅግ ጥልቅ፣ መንፈሳዊ እና ስልታዊ መሠረት ያለው ነው። ምንም እንኳን ዘመናዊው የአመራር ሳይንስ በምዕራባውያን ወይም በዓለማዊ ዩኒቨርሲቲዎች በብዛት ቢተነተንም፣የኦርቶዶክስ እምነት የሰው ልጅን ውስጣዊ ተፈጥሮ፣ የማኅበረሰብ አብሮነትን እና ከራስ ወዳድነት ነጻ የሆነ አገልጋይነትን ከመረዳት አንፃር ትልቅ እሴት አለው። በኦርቶዶክስ ሥነ-መለኮት መሠረት እያንዳንዱ ሰው በፈጣሪ መልክና አርአያ የተፈጠረ ክቡር ፍጡር ነው የሚለው ጽንሰ-ሐሳብ መሪው ከበታቹ ያሉትን ሠራተኞች በጥልቅ ክብር፣ በሰብአዊነት እና በፍትህ እንዲያስተዳድር ግዴታ ይጥልበታል። በተጨማሪም የሰው ልጅ ከፍ ወዳለ የሞራልና የመንፈሳዊ ልዕልና ደረጃ ሊደርስ እንደሚችል የሚያስረዳው የቴዎሲስ አስተስህሮ ከዘመናዊው ቀጣይነት ያለው የቪዲዮና የግል ስብዕና ዕድገት ፍልስፍና ጋር በቀጥታ ይገናኛል።
በሌላ በኩል፣ በኦርቶዶክስ ትውፊት መሰረት ቤተ ክርስቲያን የምትመራው በአንድ ሰው አምባገነናዊ ትዕዛዝ ሳይሆን በጋራ መንፈሳዊ ኅብረትና ስምምነት ወይም ሶቦርኖስት በመሆኑ መሪው ከቡድኑ ተነጥሎ የሚኖር ከፍተኛ አለቃ ሳይሆን የአካል ክፍል እንደሆነ እና እያንዳንዱ አባል እኩል ዋጋ እንዳለው ያሳያል። ይህም ከዘመናዊው አሳታፊ እና አካታች የአመራር ስልቶች ጋር ይጣጣማል። በአሁኑ ዘመን መሪዎች ከሚገጥማቸው ከባድ የውድድር ዓለም ውጥረት እና የስልጣን ጭንቀት አንጻር የኦርቶዶክስ ምስጢራዊ ትውፊት በውስጣዊ ዝምታ እና ከፈጣሪ ጋር በሚደረግ ጥልቅ ጸሎት አማካኝነት ውስጣዊ ሚዛንን መጠበቅ እንደሚያስፈልግ በሄሲካዝም አስተስህሮ ያስተምራል። ይህም መሪው በውጫዊ ውጥረትና ጫና ውስጥ ሆኖ እንኳ አእምሮውን ሰብስቦ በሰከነና በጥልቀት የማሰብ ችሎታ እንዲኖረው የሚያስችል ሲሆን ከዘመናዊው የንቃተ-ህሊና እና የአእምሮ ሰላም አስተዳደር ጋር አንድ አይነት ነው።
ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ከጥንት ጀምሮ የቆየውን እምነት፣ እሴት እና ሥርዓት ትውልድ ከትውልድ ሳታዛባ በማስተላለፍ የምትታወቅ በመሆኗ ዘመናዊው አስተዳደር ድርጅቶች ያለፉትን ስኬቶችና ውድቀቶች በማጥናት የወደፊት እቅዳቸውን እንዲያቀኑ ከሚሰጠው ምክር ጋር ይስማማል። በአጠቃላይ የኦርቶዶክስ እምነት ለዘመናዊው ዓለማዊ የአመራር ሳይንስ ያበረከተችው ትልቁ አስተዋጽኦ አመራር ማለት በቁሳቁስና በውጤት መለኪያ ብቻ የሚለካ ሳይሆን የሰውን ልጅ ሰብአዊ ክብር ከፍ የሚያደርግ፣ በኅብረትና በውይይት ላይ የተመሰረተ እንዲሁም በከባድ ውጥረት ውስጥ እንኳ ውስጣዊ ሰላምንና ጽናትን ይዞ የመገኘት ጥበብ መሆኑን ማሳየቱ ነው።
ዛዲግ አብርሀ
የአፍሌክስ ፕሬዝደንት
የቴሌግራም ቻናልችንን በመቀላቀል የአዲስ አድማስን መረጃ ይከታተሉ…

የማይክሮሶፍት መስራች ቢል ጌትስ ሮቦቶች እና አርቲፊሻል ኢንቴሊጀንስ (AI) የሰዎችን ስራ በከፍተኛ ፍጥነት እየተኩ በመሆናቸው፣ መንግስታት በነዚህ ቴክኖሎጂዎች ላይ ግብር የመጣል ውሳኔ እንዲያስቡበት ጥሪ አቀረቡ። ጌትስ ባወጡት አዲስ ጽሁፍ እንደገለፁት፣ እንደ ደንበኞች አገልግሎት፣ የህግ ረዳትነት እና ሶፍትዌር ኢንጂነሪንግ ያሉ ስራዎች በኤአይ እየተተኩ ነው፤ በቀጣይም በኮንስትራክሽን እና በሆቴል ዘርፍ ያሉ አካላዊ ስራዎች በሮቦቶች ሊወሰዱ ይችላሉ። አሁን ያለው የግብር አሰራር ኩባንያዎች ሰራተኞችን በሮቦቶች እንዲተኩ ያበረታታል፤ ምክንያቱም ሰራተኛ ሲቀጠር የሚከፈለው የደመወዝ ግብር ሮቦት ሲገዛ ስለማይከፈል ነው።

በመሆኑም በሮቦቶች እና ኤአይ አጠቃቀም ላይ ግብር እንዲጣልና የሚሰበሰበው ገንዘብ በቴክኖሎጂው ምክንያት ስራቸውን ላጡ ሰዎች መልሶ ማሰልጠኛና ድጋፍ እንዲውል ሀሳብ አቅርበዋል። ቢል ጌትስ በሮቦቶች ላይ ግብር እንዲጣል ጥሪ ሲያቀርቡ የመጀመሪያቸው አይደለም፤ እ.ኤ.አ በ2017 ሰራተኞችን በሮቦት የሚተኩ ኩባንያዎች ሰውየው ይከፍል የነበረውን ያህል ግብር ሊከፍሉ ይገባል ሲሉ ተከራክረው ነበር። አሁንም መንግስታት ከፍተኛ የስራ ማጣት ችግር ከመከሰቱ በፊት አስቀድመው ተዘጋጅተው አስፈላጊውን እርምጃ እንዲወስዱ አሳስበዋል።

የቴሌግራም ቻናልችንን በመቀላቀል የአዲስ አድማስን መረጃ ይከታተሉ…
https://t.me/AdissAdmas

*ርዕሰ መምህሩ የ900 ተማሪዎችን ህይወት ታድገዋል

በኔፓል ኑዋኮት ወረዳ በሚገኘው ትሪቡቫን ትሪሹሊ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር የሆኑት ራጄንድራ ዳዋዲ፣ አሰቃቂው ጎርፍ ትምህርት ቤቱን ከመደምሰሱ ከ10 ደቂቃ በፊት ባደረጉት ፈጣን ውሳኔ የ900 ተማሪዎችን ህይወት ታድገዋል። በዕለቱ ከጧቱ 3፡10 ላይ ጎርፍ እየመጣ መሆኑን የሚገልጹ ጥሪዎች እንደደረሷቸው፣ ለሰከንድ ሳይወላውሉ ተማሪዎቹ በፍጥነት ወደ ተራራ እንዲሸሹና ወደ ትምህርት ቤት እየመጡ ያሉ ባሶች እንዲመለሱ አዘዋል። መምህሩ “ውሳኔያችን በ10 ደቂቃ ቢዘገይ ኖሮ፣ ተማሪዎቼን ጨምሮ ሁላችንንም ዛሬ በሕይወት አታዩንም ነበር” ሲሉ አስደናቂውን አጋጣሚ ተናግረዋል።

የ16 ዓመቷ ተማሪ ዩኒሻ አማትያ እና ጓደኞቿ አደጋው ከመድረሱ ከጥቂት ሰከንዶች በፊት አምልጥዋል። ተማሪዎቹ በትምህርት ቤቱ ጀርባ ባለው ጠባብ መወጣጫ በኩል ወደ ተራራው ሲወጡ፣ ከኋላቸው የነበረው ገበያ በደቂቃዎች ውስጥ በጎርፍ ተጠራርጎ ሲወሰድ በዓይናቸው ተመልክተዋል። በተራራው ላይ ከፍ ብለው በመሸሸጋቸው ምክንያት ለሁለት ቀናት ያህል ከውጭው ዓለም ተቆራርጠው የቆዩ ቢሆንም፣ የልጅቷ አባት በስልክ ሲያገኛት በደስታ አልቅሷል። በኋላም በሄሊኮፕተር ተነስተው ወደ ቤተሰቦቻቸው ተመልሰዋል።

ይህ በእንዲህ እንዳለ፣ ከ2,400 በላይ ሰዎች በጠፉበት በዚህ አሰቃቂ የጎርፍ አደጋ ትምህርት ቤቱ ሙሉ በሙሉ በጭቃና በፍርስራሽ ተሸፍኗል። ተማሪዋ ዩኒሻ በሕይወት በመትረፏ ብትደሰትም የትምህርቷ ነገርና የጓደኞቿ መለያየት አሳስቧታል። ርዕሰ መምህር ዳዋዲ በበኩላቸው፣ ያንን አጣዳፊ ውሳኔ ባይወስዱ ኖሮ የትምህርት ቤቱ ደወል ብቻውን እንደሚቀርና ትልቅ እልቂት ይከሰት እንደነበር ገልጸዋል።

የደባርቅ ከተማን የቱሪዝም መስህብነት ለማሳደግና ጽዱ፣ ውብ እንዲሁም ለኑሮ ተስማሚ ለማድረግ የተጀመረው የኮሪደር ልማት ፕሮጀክት የበርካታ ወገኖችን ድጋፍና ትብብር በማግኘት ላይ ይገኛል። ነሐሴ 18 ቀን 2018 ዓ.ም በተካሄደው የገቢ ማሰባሰቢያ መርሃ ግብር ላይ የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ታየ አጽቀሥላሴ፣ የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አቶ አገኘሁ ተሻገር፣ የክልሉ ፕሬዚዳንት አቶ አረጋ ከበደ እንዲሁም ከፍተኛ የፌደራልና የክልል የሥራ ኃላፊዎችና ባለሀብቶች ተገኝተዋል። በዚህ ታላቅ መድረክ በጥሬ ገንዘብና በአይነት ከ450 ሚሊዮን ብር በላይ ማሰባሰብ የተቻለ ሲሆን፣ የሃብት ማሰባሰብ ሂደቱ አሁንም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተገልጿል።

በዚሁ መድረክ ታዋቂ ባለሀብቶችና ድርጅቶች ከፍተኛ አጋርነታቸውን ያሳዩ ሲሆን፣ የሬማ ኮንስትራክሽን ባለቤት አቶ ፍቅሬ 20 ሚሊዮን ብር፣ አቶ በላይነህ ክንዴ 10 ሚሊዮን ብር እንዲሁም ቢአይካ (BIKA) 15 ሚሊዮን ብር በመለገስ ግንባር ቀደም ተሳትፎ አድርገዋል። ይህ የልማት እንቅስቃሴ ደባርቅን በቱሪዝም፣ በንግድና በኢንቨስትመንት ዘርፍ የበለጠ ተወዳዳሪ የሚያደርጋት ሲሆን፣ በቀጣይም ነዋሪዎችንና የከተማዋን ወዳጆች ያካተተ ሰፊ የልማት ምዕራፍ እንደሚቀጥል የከተማዋ ልማት ኮሚቴ አስታውቋል።

የቴሌግራም ቻናልችንን በመቀላቀል የአዲስ አድማስን መረጃ ይከታተሉ…
https://t.me/AdissAdmas

*አስመጪዎች ለከፍተኛ ኪሳራ ተዳርገናል አለ

በጂቡቲ ወደብ ከ8 ወራት በላይ ቆመው በሚገኙና ግምታቸው ከ300 ሚሊዮን ዶላር በላይ በሚሆኑ ከ4,500 በላይ የከባድ ጭነትና የሕዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪዎች ምክንያት፣ አስመጪዎች ለከፍተኛ ኪሳራ መዳረጋቸውን ሪፖርተር ጋዜጣ ዘግቧል። ተሽከርካሪዎቹ ወደ አገር እንዳይገቡ የታገዱት አገሪቱ በተፈጥሮ ጋዝ አጠቃቀም መመሪያ ምክንያት በቤንዚንና ናፍጣ የሚሠሩ ተሽከርካሪዎች እንዳይገቡ በወጣው አዲስ መመሪያ ነው። በመሆኑም ከ100 በላይ አስመጪዎች ለጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ደብዳቤ በማስገባት አስቸኳይ መፍትሔ እንዲሰጣቸው ተማፅነዋል።

እንደ ሪፖርተር ጋዜጣ ዘገባ፣ የጉምሩክ ኮሚሽንም ለችግሩ መፍትሔ እንዲሰጠው የሚኒስቴር መሥሪያ ቤቶችን በተደጋጋሚ ጠይቋል። መመሪያው ከመውጣቱ በፊት ተሽከርካሪዎቹን ያዘዙት አስመጪዎች በየቀኑ ለተጨማሪ የኪራይና የወደብ ወጪ እየተዳረጉ ይገኛሉ። በተጨማሪም እገዳው በመቀጠሉ ምክንያት መንግሥት ማግኘት የሚገባውን ከ1.8 ቢሊዮን ብር በላይ የታክስ ገቢ ያጣል ተብሏል።

የቴሌግራም ቻናልችንን በመቀላቀል የአዲስ አድማስን መረጃ ይከታተሉ…
https://t.me/AdissAdmas

በኬንያ ሲካሄድ የቆየው የሁለተኛው አፍሪካ ዞን 5 ወጣቶች ኦሎምፒክ ውድድር ትናንት ምሽት ተጠናቋል። ኢትዮጵያ በውድድሩ ካስመዘገበቻቸው አጠቃላይ 12 ሜዳሊያዎች ውስጥ 6ቱን (4 ወርቅ እና 2 ብር) በአትሌቲክስ አግኝታለች።

የወርቅ ሜዳሊያዎቹን በሴቶች 800፣ 1500፣ 3000 እና 5000 ሜትር የእርምጃ ውድድር ስናገኝ፤ የብር ሜዳሊያዎቹ ደግሞ በወንዶች 1500 እና 3000 ሜትር ተመዝግበዋል።

Page 1 of 823