ልብ-ወለድ
ማክስ ኬላዳ ተብሎ የሚጠራውን ሰውዬ ገና በቅጡ ሳልተዋወቀው ልጠላው ዝግጁ ሆኜ ነበር፡፡ ጦርነቱ ገና እንደተጠናቀቀ በመሆኑ በመርከቦቹ ላይ የሚሳፈሩት ተጓዦች ከልክ በላይ በዝተዋል፡፡ አግባብ ያለው መስተንግዶ ማግኘት አስቸጋሪ ሆኗል፤ የተገኘውን ሁሉ አሜን ብሎ መቀበል ግድ ነበር፡፡ አንድ ክፍል ለብቻ ማግኘትማ…
Read 3528 times
Published in
ልብ-ወለድ
ሊቀ ጉባኤ ነሲቡ አያሌው ደጃፍ ላይ ቁጭ ብለው ይተክዛሉ፡፡ ከጎጇቸው ደብዳቤውን ለሶስተኛ ጊዜ አነበቡት፡፡ አንብበውት ሲጨርሱ፣ የእስቴን ተራሮች አሻግረው እያዩ በረጅሙ ተነፈሱ፡፡ ከተራሮቹ በስተጀርባ፣ ልጃቸው ምሳሌ ይታያቸዋል፡፡ እቅፍ አበባ ይዞ፣ እያሰቀለለ ሲጠብቃቸው ይታያቸዋል። ለክብር የታጨ ልጃቸው፣ የእሳቸውን መምጣት ናፍቆ፣ መንገድ…
Read 4532 times
Published in
ልብ-ወለድ
እነዚያ በክዋክብት መሀል የተሞሸሩ የሚመስሉ ዓይኖችዋ መኝታዬ ድረስ መጥተው ሲንቦገቦጉ፣አልጋዬን አልፈው ልቤ ለብቻዋ አገላብጠው ሲጠብሷት መነሳት ግድ አለኝ፡፡ ነፍሴ ብቻዋን እስክስታ እየመታች፣ በሳቅዋ ደወል ትዝታ ስትሰክር ውሎ ማደር ለምዶባታል፡፡ ግን በጧት ከባድ ነው፡፡ ገና ጀንበር ቅንድብዋን ሳትገልጥ፣ ገና አድማሳት በብርሃን…
Read 15895 times
Published in
ልብ-ወለድ
ሰንበትን በዚያ ባለፈ ባገደመ ቁጥር ያያቸዋል -ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን ቅጽር ስር፤ መናኛ ልብስ ለብሰው ባነጠፋት ጨርቅ ላይ ሲመፀወቱ፡፡ …ፈፅሞ ያላሰበው ቦታ ላይ ነው ያያቸው፤ ኮከብ ቆጣሪም ሊገምተው የማይችል የመሰለው ቦታ ላይ፡፡ ለማመን ተቸግሮ ነበር፡፡ ግንባራቸው ላይ የተጋደመው ጠባሳ ነው ጥርጣሬውን የከላት።…
Read 4146 times
Published in
ልብ-ወለድ
አንገቱ ላይ የተንጠለጠለውን ገመድ የሙጥኝ እንዳለ ነው፡፡ ቁርጠኛ ውሳኔውን ለማጨናገፍ የሚንከወከው ድንገቴ ቢመጣ ሳይቀድመው እንደሚቀድመው ተማምኗል፡፡ አንዲት እራፊ ጨርቅ ብቻ ነች ኃፍረተ - ሥጋውን የሸፈነችው፡፡ ገመዷ ከቦታዋ መኖር አለመኖሯን እያሰለሰ ይሰልላታል፡፡ጠደፍ ጠደፍ እያለ ሠፊውን ጎዳና በሰጎን ቅልጥሞቹ እየመተረ ማቋረጥ ጀመረ፡፡…
Read 4452 times
Published in
ልብ-ወለድ
እሣት እንደናፈቀው ምድጃ ፊቱ ቀዝቃዛ ነው። አይኖቹ እሣት አይወረውሩም፡፡ ይልቅ በረዶ ይረጭባቸዋል፡፡ ጥርሶቹ ብዙ ጊዜ ባይገለጡም አንዳንዴ ለቀቅ ሲያደርጋቸው፣ ክርክም ብለው የተደረደሩ ናቸው፡፡ ግን የትምባሆ ጢስ ፈርሞባቸው ያን ያህል ትኩረት አይስቡም፡፡ መርመራ ዳንሣሞን ያለ መጥረቢያ ማየት ይናፍቃል፡፡ ጧት ሻይ ቤት፣…
Read 3934 times
Published in
ልብ-ወለድ