Administrator

Administrator

ኢትዮ ቴሌኮምና የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ከትላንት በስቲያ የተፈራረሙት ስምምነት፣ የሚኒስቴር መ/ቤቱን የኦፕሬሽንና አገልግሎት አሰጣጥን ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር በማስቻል፣ የውሃና ኢነርጂ ሃብቶችንና መሰረተ-ልማቶችን በዘመናዊና ቀልጣፋ ቴክኖሎጂ በማገዝ ውጤታማነትን የሚያሳድግ አሰራር በጋራ ለመተግበር ያስችላል ተብሏል።
ይህ ስትራቴጂያዊ ስምምነት፣ በዋናነት የኢትዮ ቴሌኮምን ዘመናዊ የክላውድ መሰረተ ልማትን በመጠቀም፣ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴርና በሥሩ የሚገኙ ተቋማትን መረጃ ዲጂታል ለማድረግ የሚያስችል መሆኑ ተጠቁሟል፡፡
 
በተጨማሪ፤ በፌደራልና በክልል ደረጃ የሚገኙ መ/ቤቶችን ማለትም፡- በክልል፣ በዞን፣ በወረዳና በቀበሌ ደረጃ የሚገኙ የውሃ ጽ/ቤቶችን በቴክኖሎጂ በማስተሳሰር የዳታና የመረጃ ልውውጥ በወቅቱ ለማድረግ ከፍተኛ ጠቀሜታ ይኖረዋል ተብሏል።
ስምምነቱ፣ የስማርት አገልግሎት ሶሉሽኑን ከመረጃ ማዕከላት ጋር በማስተሳሰር፣ ወደ ውስጥና ወደ ውጭ የሚፈሱ እንዲሁም የውሃ ሙሊት ደረጃዎችን በተፈለገው ቅጽበት ለመቆጣጠር የሚያስችሉ ሶሉሽንስ መተግበርን የሚያካትት ሲሆን፤ የተቋማት፣ የንግድና የግል ደንበኞች ውሃ ቆጣሪዎችን ዲጂታል ማድረግ ላይም ያለመ መሆኑ ተጠቁሟል።
 
የአጋርነት ስምምነቱ፣ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴርንና በስሩ የሚገኙ የተጠሪ ተቋማትን የአሰራር ጥራት፣ ፍጥነትና ውጤታማነት ለማሳደግ፣ በመረጃ ላይ የተመሠረተ ውሳኔ አሰጣጥ እንዲኖር ለማስቻል፣ የአገልግሎት አሰጣጡን አስተማማኝነትና ዘላቂነት ለማረጋገጥ ትልቅ ሚና እንደሚጫወት የተገለጸ ሲሆን ከዚህም ባሻገር፣ የደንበኞችን የክፍያ ሥርዓት ዲጂታል ማድረግን ጨምሮ፣ በሁሉም የፕሮጀክቱ ዘርፎች ላይ ሁለገብ ሙያዊ ድጋፍ መስጠትን ያካትታል ተብሏል፡፡
 
በዚህ ስምምነት መሠረት፣ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር፣ ለኢትዮ ቴሌኮም አስፈላጊ የሆኑ ዳታዎችን፣ መረጃዎችንና ሰነዶችን የሚያቀርብ ሲሆን፣ ኢትዮ ቴሌኮም በበኩሉ በስምምነት ማዕቀፉ ውስጥ በተገለጸው መሠረት ቴክኖሎጂዎችን ማቅረብ፣ ዲጂታል ሶሉሽኖችን መትከልና ማስፋፋት፣ አስፈላጊውን ዳታና መረጃ ለውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ማጋራት፣ የቴክኒክ ድጋፍና የአቅም ግንባታ ስልጠና መስጠትና አመቺ የክፍያ ዘዴዎችን ማዘጋጀት እንዲሁም ከፍተኛ ጥራት ያላቸውና ቀልጣፋ የዲጂታል መሠረተ ልማቶችን የሚያቀርብ እንደሚሆን ተመልክቷል።
የቴሌግራም ቻናልችንን በመቀላቀል የአዲስ አድማስን መረጃ ይከታተሉ…
Wednesday, 08 November 2023 00:00

ዜና - ሹመት

ላለፈው አንድ ዓመት በፕላንና ልማት ሚኒስቴር፣ ሚኒስትር ዴኤታ ሆነው ሲሰሩ የቆዩት አቶ ሳንዶካን ደበበ፤ የጠቅላይ ሚኒስትር ልዩ ጽህፈት ቤት ኃላፊ (chief of staff) ሆነው ተሾሙ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ፣ በሚኒስትር ዴኤታ ማዕረግ፣ የልዩ ጽህፈት ቤታቸውን እንዲመሩ አቶ ሳንዶካንን የሾሟቸው፤ ከሦስት ሳምንት በፊት መሆኑን ለማወቅ ተችሏል፡፡

በሌላ በኩል፤ ለአዲስ አበባ  ቤቶች ልማትና አስተዳደር ቢሮ የተለያዩ ክፍሎች፣ ሦስት አዳዲስ ሃላፊዎች ተሹመዋል፡፡ ኢንጂነር ስጦታው አካለ፣ በአዲስ አበባ  ቤቶች ልማትና አስተዳደር ቢሮ፣ የቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን የግንባታ ዘርፍ ም/ዋና ዳይሬክተር ሆነው የተሾሙ ሲሆን፤ ኢንጂነር ቶማስ ደበሌ፣ በአዲስ  አበባ  ቤቶች ልማትና አስተዳደር ቢሮ፣ የቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን የቤት ማስተላለፍ ዘርፍ ም/ዋና ዳይሬክተር ሆነው ተሹመዋል።

አቶ ሙሉነህ ፈይሳ ደግሞ የአዲስ አበባ ቤቶች ልማትና አስተዳደር ቢሮ፣ የቤት ልማትና አሰራር ስርአት ዘርፍ ም/ቢሮ ኃላፊ ሆነው መሾማቸው ታውቋል፡፡

ኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር (ኢመደአ) እና የኢትዮ ቴሌኮም በጋራ ለመሥራት በሚያስችላቸው ጉዳዮች ላይ ሰፊ ውይይት አደረጉ።
በውይይቱ ወቀት የኢመደአ ዋና ዳይሬክተር አቶ ሰለሞን ሶካ በኢመደአ የእድገት ጉዞ ውስጥ የቴሌኮም አሻራ ከፍተኛ መሆኑን ገልጸው ሁለቱ ተቋማት ትብብራቸዉን ወደ ላቀ ደረጃ በማሳደግ በቅንጅት መስራት መቻላቸዉ ለሀገራዊ እድገት ያለዉ አስተዋጽዎ ከፍተኛ መሆኑን አንስተዋል።
ሁለቱ ተቋማት በጋራ የሚሰሩባቸዉ ብዙ ጉዳዮች እንዳሉ የጠቆሙት ዋና ዳይሬከተሩ አቶ ሰለሞን ዲጂታል 2025ን እንደ መነሻ በመዉሰድ ለሃገራዊ የዲጂታል ሽግግር የብኩላችንን ሚና መጫወት ይገባናል ብለዋል።
በትብብር መስራት ከቻልን ከሀገር አልፈን በመካከለኛው ምስራቅ እና በአፍሪካ በቢሊየን የሚቆጠር ትርፍ ሊያስገኝ የሚችል ምርትና አገልግሎቶች በሁለቱም ተቋማት ዉስጥ መኖሩን የገለጹት ዋና ዳይሬክተሩ እነዚህን ምርትና አገልግሎቶች ለገበያ በማቅረብ በዘርፉ የሃገርን ኢኮኖሚ መደገፍ እንችላለን ብለዋል።
ዘመኑ የመደመር በመሆኑ በተናጠል መሮጥ ብዙም አዋጭ አለመሆኑን የጠቆሙት አቶ ሰለሞን ሶካ ኢመደአ እና ኢትዮ-ቴሌኮም ተባብሮ በመስራት፤ የሃብት ብክነትን በመቀነስ፤ ሀገር በቀል ቴክኖሎጂዎችን በማልማትና ደረጃቸዉን ከፍ አደርጎ ወደ ገበያ በማቅረብ፤ ሀገራዊ ሀብት መፍጠር እንደሚገባ ጠቁመዋል።
የኢትዮ-ቴሌኮም ዋና ሥራ አሥፈጻሚ ፍሬህይወት ታምሩ በበኩላቸው ይህ ውይትት ቢዘገይም ያልረፈደ በመሆኑ በቀጣይ በትብብር የምንሰራቸዉ ስራዎችን በመለየት ለሀገር የሚጠቅሙ ስራዎችን መስራት እንችላለን ብለዋል።
ኢመደአ ለሀገር ሰፊ ሀብት የሚሆኑ ምርትና አገልግሎት እንዳለዉ ተረድቻለሁ ያሉት ዋና ስራ አስፈጻሚዋ በሂደት ምርትና አገልግሎቶቹ በአለም አቀፍ ስታንዳርድ መሰረት ከፍ በማድረግና በጋራ በመስራት ትርፋማ መሆን እንደሚቻል ጠቁመዋል።
በኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር በነበረዉ ቆይታ የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ስራ አስፈጻሚ ፍሬህይወት ታምሩን ጨምሮ ሌሎች የኢትዮ-ቴሌኮም ከፍተኛ አመራሮች በኢመደአ ዋና መስሪያ ቤት እየተሰሩ ያሉ ስራዎችን ጎብኝተዋል።


•  ተቋሙ በአፍሪካ የአይቲ ማዕከል ለመሆን እየሰራ መሆኑ ተጠቁሟል


በአፍሪካ የአይቲ ማዕከል ለመሆን ራዕይ ሰንቆ በአዲስ መልክ እየተዋቀረና እየተደራጀ መሆኑ የተነገረለት የአይቲ ፓርክ ኮርፖሬሽን፤ ከሁለት ሳምንት በኋላ በይፋ  ሥራ እንደሚጀምር ተገለጸ፡፡ በአይቲ ፓርኩ፣ በኢትዮጵያ የመጀመሪያ  የሆነው  የግል  የዳታ ማዕከል አገልግሎት መስጠት መጀመሩም ተጠቁሟል፡፡

ይህ ይፋ የተደረገው በዛሬው ዕለት ጠዋት በሸራተን አዲስ ሆቴል፣ “የዳታ ማዕከል አገልግሎት ሥነምህዳር ዕድሎችን ለፋይናንስ ዘርፉና ለቴክኖሎጂ ኢንዱስትሪው ማመቻቸት” በሚል ርዕስ፣ ለግማሽ ቀን በተካሄደ ጉባኤ ላይ ሲሆን፤ ጉባኤውን የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር፣ የአይቲ ፓርክ ኮርፖሬሽንና የዊንጉ አፍሪካ ዳታ ማዕከል  በትብብር እንዳዘጋጁት ታውቋል፡፡

የአይቲ ፓርክ ኮርፖሬሽኑን  የሚያስተዳድረው የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትሩ ዶ/ር በለጠ ሞላ በጉባኤው መክፈቻ ላይ እንደገለጹት፤የኢትዮጵያን የዲጂታል ሽግግር እውን በማድረግ ረገድ አይቲ ፓርኩ ጉልህ ሚና የሚጫወት ይሆናል፡፡ ከዚህ አንጻር ጉባኤው ወቅታዊና ተገቢ መሆኑን ሚኒስትሩ አስምረውበታል፡፡

የአይቲ ፓርክ ኮርፖሬሽን ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ሔኖክ አህመድ በበኩላቸው በሰጡት ማብራሪያ፣ የኮርፖሬሽኑ ትልቁ ዓላማው ቢዝነስ መሥራት የሚያስችል ሥነምህዳር መፍጠር መሆኑን ጠቁመው፤ ለዚህም ሁሉም በጋራ የሚጠቀምበት ሪሶርስ በአንድ ቦታ ያቀርባል ብለዋል፡፡

ራዕያችን የአፍሪካ የአይቲ ማዕከል መሆን ነው ያሉት ዋና ሥራ አስፈጻሚው፤ ይህን ለማሳካትም  የቴክኖሎጂ ሽግግርን በማምጣትና አቅምን በማሳደግ ዓለማቀፍ ተወዳዳሪነትን ማጎልበት እንደሚያስፈልግ አጽንኦት ሰጥተው ተናግረዋል፡፡

በዛሬው ጉባኤ ላይ  በኢትዮጵያ የመጀመሪያውን የግል የዳታ ማዕከል፣ በአይቲ ፓርክ ገንብቶ አገልግሎት መስጠት መጀመሩን የጠቆመው ዊንጉ አፍሪካ የዳታ ማዕከል ኩባንያ፤ በምሥራቅ አፍሪካ ኢትዮጵያ፣ ጅቡቲ፣ ሶማሊላንድና ታንዛንያን  ጨምሮ በአራት አገራት በዘርፉ አስተማማኝ አገልግሎት እየሰጠ  የሚገኝ ስመ-ጥር ኩባንያ ነው ተብሏል፡፡   

ኩባንያቸው በቀጣናው ተጠቃሽ  የዳታ ማዕከል አገልግሎት አቅራቢ መሆኑን የገለጹት የዊንጉ አፍሪካ ዳታ ማዕከል  ካንትሪ ዳይሬክተር አቶ ተሾመ፤ በኢትዮጵያም ዓለማቀፍ ደረጃውን የጠበቀ አስተማማኝ የዳታ ማዕከል መገንባቱን ጠቁመው፤ በዋናነት  የፋይናንስ ዘርፉና የቴክኖሎጂ ተቋማት የአገልግሎቱ ተጠቃሚ እንደሚሆኑ ተናግረዋል፡፡

ዊንጉ አፍሪካ ወደ ኢትዮጵያ ገብቶ ሥራ ከጀመረ 18 ወራት ማስቆጠሩን የጠቆሙት ዳይሬክተሩ፤ የዚህ ጉባኤ አንዱ ዓላማ እነዚህ የፋይናንስና ቴክኖሎጂ ተቋማት ከፍተኛ ወጪ አውጥተው፣ የየራሳቸውን የዳታ ማዕከል ከመገንባት ይልቅ በኛ ማዕከል ቢጠቀሙ፣ የበለጠ እንደሚያዋጣቸው መረጃና ግንዛቤ ለመስጠት ነው ብለዋል፡፡ ጉባኤው አጋርነትና ትብብር የመፍጠሪያ መድረክ እንደሚሆንም ጨምረው አመልክተዋል፡፡
የዳታ ማዕከሉን ከሚመሩት ውስጥ 90 በመቶው ኢትዮጵያውያን መሆናቸው የገለጹት የኩባንያው አመራሮች፤ ማዕከሉ ለወጣት ኢትዮጵያውያን የቴክኖሎጂ ኢንጂነሮች ትልቅ የሥራ ዕድል መፍጠሩን አውስተዋል፡፡

የዘርፉ ዓለማቀፍ ተዋናዮች በአጋርነት አብረውን እንዲሰሩ መሳብ ችለናል ያሉት አመራሮቹ፤ የመንግሥት ደንብና መመሪያዎች ወጥተው እንደተጠናቀቁ እኒህ ተዋናዮች ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ ገልጸዋል፡፡ ማይክሮሶፍት፣ ቲክቶክና ሜታ (የቀድሞው ፌስቡክ) የመሳሰሉ ግዙፍ ዓለማቀፍ የቴክኖሎጂ ኩባንያዎች ወደዚህ አገር እንዲመጡም እየሰራን ነው ብለዋል - የዊንጉ አፍሪካ ዳታ ማዕከል ኩባንያ  አመራሮች፡፡

የዊንጉ አፍሪካ ዳታ ማዕከል፣ በ50 ሚሊዮን ዶላር ወጪ መገንባቱ  ይታወቃል፡፡

በዚህ ለግማሽ ቀን በሸራተን አዲስ በተካሄደው ጉባኤ ላይ፣ የአይቲ ኢንዱስትሪው መሪዎች፣ የመንግሥት ከፍተኛ ባለሥልጣናትና የፋይናንስ ተቋማት አመራሮች ተሳትፈዋል፡፡

የአምራች ኢንተርፕራይዞች አገር አቀፍ ኤግዚቢሽንና ባዛር ለ5 ቀናት ይካሄዳል


•  ኤግዚቢሽንና ባዛሩ ታህሳስ 3 በስካይ ላይት ሆቴል ይከፈታል


”ኢትዮጵያ ታምርት፤ እኛም እንሸምት” በሚል መሪ ቃል፣ ”የኛ ምርት” የተሰኘ የአምራች ኢንተርፕራይዞች አገር አቀፍ ኤግዚቢሽንና ባዛር፣ ከታሕሳስ 3 እስከ ታሕሳስ 7 ቀን 2016 ዓ.ም በስካይ ላይት ሆቴል እንደሚካሄድ ተገለጸ፡፡

የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት አመራሮችና የፕራና ኢቨንትስ ዳይሬክቲንግ ማናጀር፣ ኤግዚቢሽንና ባዛሩን አስመልክቶ ዛሬ ጠዋት ረፋዱ ላይ በስካይ ላይት ሆቴል ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል፡፡

”የኛ ምርት” የተሰኘው ኤግዚቢሽንና ባዛር ዋና ዓላማ፣ አምራች ኢንተርፕራይዞች በምርት ትውውቅ፣ በምርት ሽያጭ፣ በገበያ ትስስር፣ በቴክኖሎጂ ሽግግር፣ በልምድና የመረጃ ልውውጥ የተሻለ አቅም መፍጠርና የዘርፉን ፋይዳ  ማሳየት የሚያስችላቸውን መድረክ መፍጠር ነው ተብሏል፡፡

በዚህ ኤግዚቢሽንና ባዛር፣ ከመላ አገሪቱ የተውጣጡ ከ100 በላይ የጨርቃጨርቅና አልባሳት ውጤት አምራቾች፣ የፕላስቲክ ውጤት አምራቾች፣ የቆዳና የቆዳ ውጤት አምራቾች፣ የአግሮ ፕሮሰሲንግ አምራቾች፣ የኬሚካል ውጤት አምራቾች፣ የማዕድንና ጌጣጌጥ ውጤት አምራቾች፣ የእንጨትና ብረታ ብረት ውጤት አምራቾችና ሌሎች ዋና ድጋፍ ሰጪ ተቋማት የሚሳተፉበት ሲሆን፤ ከ50ሺ በላይ ገዢና ጎብኚዎች ይስተናገዱበታል ተብሎ ይጠበቃል፡፡

ኤግዚቢሽንና ባዛሩ፣ ከመላው ኢትዮጵያ የተውጣጡ ውጤታማ  የአገር ውስጥ አምራች ኢንተርፕራይዞች በአንድ ጣሪያ ሥር ተሰባስበው ከመላ አገራችን ከሚመጡ የህብረተሰብ ክፍሎችና ከአጋር ተቋማት ጋር የገበያ ትስስር ለመፍጠር የሚያስችል፣ ልምድና ተሞክሮ ለመጋራት ምቹ ዕድል የሚፈጥር እንዲሆን ለማስቻል ጥረት መደረጉ የተገለጸ ሲሆን፤ በተጨማሪም፣ አምራቾች የደረሱበትን የቴክኖሎጂና የምርት የእድገት ስኬት ደረጃ፣ ልምድና ተሞክሮ የሚያካፍሉበት እንዲሁም በዘርፉ ጥናት ያደረጉ ምሁራን ጥናታዊ ጽሁፍ የሚያቀርቡበትና የፓናል ውይይት የሚካሄድበት መድረክ እንደሚሆንም ለማወቅ ተችሏል፡፡


”የኛ ምርት” ኤግዚቢሽንና ባዛር፣ ዘላቂ የንግድ ትስስርን ለመፍጠርና የምርት ዕድገትን ለማረጋገጥ በሚያስችል መልኩ በጥንቃቄ የታቀደ ነው የተባለ ሲሆን፤ ለተሳታፊዎች የንግድና የምርት ስኬት የሚተጋ ከመሆኑም በላይ የአምራች ኢንተርፕራይዞች ምርቶችን ማህበረሰቡ በአገር ምርት እንዲኮራና ትኩረት ሰጥቶ እንዲሸምት ምቹ ሁኔታ የሚፈጥር ልዩ ኹነት መሆኑ ተጠቁሟል፡፡

”የኛ ምርት” የተሰኘውን አገር አቀፍ  ኤግዚቢሽንና ባዛር፣ የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት እና ፕራና ኤቨንትስ በትብብር እንደሚያዘጋጁት ታውቋል፡፡

Monday, 06 November 2023 19:09

1242.pdf addisadmassnews

https://online.fliphtml5.com/etocz/zlhw/

የአዲስ አበባ ባህል፣ ኪነ-ጥበብና ቱሪዝም ቢሮ ከሚሰራቸዉ ዋና ዋና ተግባራት መካከል ከኪነ-ጥበብ ባለሙያዎችና በዘርፉ ውስጥ ካሉ አካላት ጋር ኪነ-ጥበብን በተለያዩ መንገዶች ማሳደግና በኪነ-ጥበብ የተገነባ ትውልድን ማፍራት ነዉ።
በዚሁ መሰረት የኢትዮጵያ ቴአትር ባለሞያዎች ማህበር ከቢሯችን፣ ከኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽንና ከቢ ኘላስ ጋር በመተባበር የተዘጋጀ የቴአትር እና ቴሌቪዥን ፌስቲቫል የኪነ-ጥበብ ባለሙያዎችና የቴአትር ተማሪዎች በተገኙበት ለአራተኛ ጊዜ እየተካሄደ ነዉ።
ፌስቲቫሉ ቦሌ በሚገኘው ፍሬንድሺፕ ሆቴል እና ሸጎሌ ባለው አዲሱ የኢቢሲ ሚዲያ ኮምፕሌክስ ውስጥ ይካሄዳል።
በአዲስ አበባ ባህል፣ ኪነ-ጥበብና ቱሪዝም ቢሮ (የኪነ-ጥበብ ሐብቶች ልማት፣ መድረኮችና ኩነቶች ዝግጅት ዳይሬክተር ) አቶ ሰለሞን ደኑ ቢሮው ከኢትዮጵያ ቴአትር ማህበርና ከሌሎች የኪነ-ጥበብ ባለድርሻዎች ጋር በትስስር በመስራት ኪነ-ጥበባዊ ጥናትና ዉይይቶች እየቀረቡ ለህዝብ መድረሳቸው ለዘርፉ የመረጃ ፍሰትን ያዳብራል ብለዋል።
በተጨማሪም ቢሮዉ ቀጣይ ይህን መሰል ፕሮግራም በማስተባበር እንደሚሰራ አሳዉቀዋል።
ዛሬ ጥቅምት 24 /2016 ዓ.ም የቴአትርና ቴሌቪዥን ፌስቲቫል ላይ "የአዛውንቶች ክበብ" የተሰኘዉ ተዉኔት ታሪክ አወቃቀርና አጠቃላይ ገለፃ ተደርጎል።
ከዛሬ አርባ ዓመታት በፊት በፀኃፊ ተውኔት ነጋሽ ገ/ማርያም የተደረሰዉ "የአዛውንቶች ክበብ" ቴአትር በሀገራችን አንጋፋ በሆኑት በአውላቸዉ ደጀኔ፣ ወጋየሁ ንጋቱ እና በሌሎች ዕውቅ ተዋኒያን ተተዉኗል።
"የአዛዉንቶች ክበብ" ቴአትር በኢትዮጵያ የቴአትር ታሪክ ዉስጥ ትልቅ ሚና የጣለ እንደሆነ የቴአትር ባለሙያዎች ማህበር ፕሬዚደንት ቢኒያም ወርቁ አንስተዋል።
ድርሰት እና አጠቃላይ ታሪኩን የሚመለከት ጥናት በባለሙያ ቀርቦ ዉይይት ተደርጎበታል።
ቀጣይ በሚካሄደው የቴአትር ፌስቲቫል በገጣሚ ታረቀኝ በዳሳ የተደረሰዉ "የሁለት ክፍል ግብዣ" የተሰኘዉ ተውኔት ጥናትና ውይይት ሸጎሌ በሚገኘዉ በኢቲቪ አዲሱ የሚዲያ ኮምፕሌክስ ይቀርባል ነዉ የተባለዉ።
ሌሎች የቀደምት ተውኔቶች በመድረክ ድጋሜ እየቀረቡ ለህዝብ ቢቀርቡ የሚሉ ሀሳቦች ተነስተዋል።
የኢትዮጵያ ቴአትር ባለሞያዎች ማህበር ጥያቄዉን በመዉሰድ እንደሚሰራ አሳዉቋል።
የአርካይቪንግ እና ዶክመንቴሽን ስራዎች ላይ ጥንቃቄ ሊደረግባቸዉ እንደሚገባ ተነስቷል።
በተለይም ዲጂታል በሆነ መንገድ ቢቀመጡ በተፈለጉ ሰዓት መገኘት የሚችሉበት ሁኔታ ቀላል አማራጭ እንደሚሆን ኤርሚያስ ፍቅሬ/ጥናት አቅራቢ/ አንስተዋል።
የሁለቱ ተውኔቶች ጥናትና ውይይት በዋናነት የአርባኛ ዓመት መታሰቢያ ዘመናቸውን ምክንያት በማድረግ በትብብር የተዘጋጀ ሲሆን ሌሎች የተውኔት ስራዎችን ለመዘከር ያግዛል ተብሏል።
(ባ/ኪ/ቱ ቢሮ)
አትሌት ታምራት ቶላ በኒው ዮርክ በተካሄደው የማራቶን ውድድር አሸናፊ መሆን ችሏል፡፡
አትሌት ታምራት ውድድሩን ለማጠናቀቅ 2 ሰዓት ከ4 ደቂቃ ከ58 ሰኮንድ የፈጀበት ሲሆን፤ የገባበት ሰዓትም በኒው ዮርክ ማራቶን ውድድር ታሪክ አዲስ ክብረ ወሰን ሆኗል፡፡
በውድድሩ ሌላኛው ኢትዮጵያዊ አትሌት ሹራ ቂጣታ ሶሰትኛ ደረጃን ይዞ አጠናቋል::
በሴቶቹ በኩል አትሌት ለተሰንበት ግደይ የኒው ዮርክ ማራቶን ውድድር ሁለተኛ በመሆን ስታጠናቅቅ፤ ኬኒያዊቷ አትሌት ሄለን ኦቢሪ አንደኛ በመውጣት ውድድሩን አሸንፋለች::

የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት ረዳት ኮሚሽነር ደራርቱ ቱሉ ከጃፓን መንግስት ለውጭ ሀገር ዜጎች የሚሰጠውን የሀገሪቱን ከፍተኛ የክብር ሽልማት ተበረከተላት።

ሽልማቱ የተበረከተላት በኢትዮጵያና ጃፓን መካከል ያለው የስፖርት ዲፕሎማሲ እንዲጠናከር ላደረገችው አስተዋጽኦ መሆኑም ተገልጿል።

አትሌት ደራርቱ የቀድሞ የጃፓን ጠቅላይ ሚኒስቴር ሺንዞ አቤ በፈረንጆቹ 2014 ኢትዮጵያን በጎበኙበት ወቅት ከኢትዮጵያውያን አትሌቶች ጋር እንዲወያዩ እድርጋ እንደነበር ተመላክቷል፡፡

በአውሮፓውያኑ 2019 ላይም ደራርቱ የጃፓን ስፖርት ኤጀንሲ ኮሚሽነር ከሆኑት ሱዙኪ ዳይቺን እና የቶኪዮ ኦሎምፒክ ሃላፊ ሃሺሞቶ ሴይኮ ጋር በመምከር የልምድ ልውውጥ ማድረጓ ተገልጿል፡፡

ለረዳት ኮሚሽነር ደራርቱ ቱሉ የተሰጠው ይህ እውቅናና ሽልማት እኤአ ከ1875 ጀምሮ ለውጭ ሃገር ዜጎች በጃፓን መንግስት የሚሰጥ አንጋፋ የክብር ሽልማት መሆኑን በኢትዮጵያ የጃፓን ኤምባሲ መረጃ አመልክቷል።

ይህ ሽልማት የውጭ ሀገር ዜጎች በጃፓን እና በሌሎች ሀገራት መካከል ያለውን ወዳጅነት ለማሳደግ ላበረከቱት አስተዋፅኦ የሚሰጥ ሲሆን፤ ረዳት ኮሚሽነር ደራርቱ ቱሉም ይህን ከፍተኛ የክብር ሽልማት በማገኝት የመጀመሪያዋ ኢትዮጵያዊት ሆናለች።

አንጋፋው ደራሲ፣ ገጣሚ፣ ሀያሲ፣ ተዋናይ፣ ዳይሬክተር... ጋሽ ስዩም ተፈራ በአዲስ አበባ ባህል፣ ኪነ-ጥበብና ቱሪዝም ቢሮ እና ሰምና ወርቅ ሚዲያና ኢንተርቴይመንት በጋራ በመሆን በተዘጋጀው መድረክ ላይ የጥበብ አፍቃርያን ፣ አንጋፋ አርቲስቶች በተገኙበት የምስጋና መድረክ ዛሬ ጥቅምት 24/2016 ዓ.ም በኢትዮጵያ የባህል አምባሳደር ዮድ አቢሲኒያ ባህላዊ የምግብ አዳራሽ የምስጋና አዋርድና በክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ የተሸለሙትን ለአንጋፋ አርቲስቶች ያበረከቱት ኒሻን ጨምሮ የተለያዩ ሽልማቶች ተበርክቶለታል።
በሀገራችን የትወና ሙያ የጎላ አሻራና ማህተም ያሳረፈ ታላቁ አርቲስት ጋሽ ስዩም ተፈራ በሀገራችን ኢትዮጵያ የኪነ ጥበብ ስራ
ዎች ለማሳደግ የተለያዩ የጥበብ ሰራዎች በመስራት አስተዋፅኦ ካደረጉ እውቅ አርቲስቶች አንዱና በተለያዩ የኪነ-ጥበብ ሙያዎች 50 አመታትን ያገለገለና ለሀገራችን የኪነ-ጥበብ እድገት የታገለ የተመሰከረለት አርቲስት ነው።በዚህ የምስጋና መድረክም ጋሽ ስዩም የፃፋቸውን 3 መፅሓፎችን በይፋ አስመርቀዋል።
 
በፕሮግራሙም ጋሽ ስዩም ታምሞ በነበረበት ወቅት ድጋፍ ላደረገለት የኢትዮጵያ ህዝብና ግለሰቦች እንዲሁም የህክምና ተቋማት ምስጋና አቅርበዋል።
Page 6 of 676