
Administrator
ኢትዮ ቴሌኮምና የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የስማርት አገልግሎት ሶሉሽንስ ተግባራዊ ለማድረግ የሚያስችል ስምምነት ፈጸሙ
ዜና - ሹመት
ላለፈው አንድ ዓመት በፕላንና ልማት ሚኒስቴር፣ ሚኒስትር ዴኤታ ሆነው ሲሰሩ የቆዩት አቶ ሳንዶካን ደበበ፤ የጠቅላይ ሚኒስትር ልዩ ጽህፈት ቤት ኃላፊ (chief of staff) ሆነው ተሾሙ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ፣ በሚኒስትር ዴኤታ ማዕረግ፣ የልዩ ጽህፈት ቤታቸውን እንዲመሩ አቶ ሳንዶካንን የሾሟቸው፤ ከሦስት ሳምንት በፊት መሆኑን ለማወቅ ተችሏል፡፡
በሌላ በኩል፤ ለአዲስ አበባ ቤቶች ልማትና አስተዳደር ቢሮ የተለያዩ ክፍሎች፣ ሦስት አዳዲስ ሃላፊዎች ተሹመዋል፡፡ ኢንጂነር ስጦታው አካለ፣ በአዲስ አበባ ቤቶች ልማትና አስተዳደር ቢሮ፣ የቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን የግንባታ ዘርፍ ም/ዋና ዳይሬክተር ሆነው የተሾሙ ሲሆን፤ ኢንጂነር ቶማስ ደበሌ፣ በአዲስ አበባ ቤቶች ልማትና አስተዳደር ቢሮ፣ የቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን የቤት ማስተላለፍ ዘርፍ ም/ዋና ዳይሬክተር ሆነው ተሹመዋል።
አቶ ሙሉነህ ፈይሳ ደግሞ የአዲስ አበባ ቤቶች ልማትና አስተዳደር ቢሮ፣ የቤት ልማትና አሰራር ስርአት ዘርፍ ም/ቢሮ ኃላፊ ሆነው መሾማቸው ታውቋል፡፡
የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር እና ኢትዮ ቴሌኮም በጋራ መሥራት በሚችሉባቸው ጉዳዮች ላይ ተወያዩ
አይቲ ፓርክ ከሁለት ሳምንት በኋላ በይፋ ሥራ እንደሚጀምር ተገለጸ
• ተቋሙ በአፍሪካ የአይቲ ማዕከል ለመሆን እየሰራ መሆኑ ተጠቁሟል
በአፍሪካ የአይቲ ማዕከል ለመሆን ራዕይ ሰንቆ በአዲስ መልክ እየተዋቀረና እየተደራጀ መሆኑ የተነገረለት የአይቲ ፓርክ ኮርፖሬሽን፤ ከሁለት ሳምንት በኋላ በይፋ ሥራ እንደሚጀምር ተገለጸ፡፡ በአይቲ ፓርኩ፣ በኢትዮጵያ የመጀመሪያ የሆነው የግል የዳታ ማዕከል አገልግሎት መስጠት መጀመሩም ተጠቁሟል፡፡
ይህ ይፋ የተደረገው በዛሬው ዕለት ጠዋት በሸራተን አዲስ ሆቴል፣ “የዳታ ማዕከል አገልግሎት ሥነምህዳር ዕድሎችን ለፋይናንስ ዘርፉና ለቴክኖሎጂ ኢንዱስትሪው ማመቻቸት” በሚል ርዕስ፣ ለግማሽ ቀን በተካሄደ ጉባኤ ላይ ሲሆን፤ ጉባኤውን የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር፣ የአይቲ ፓርክ ኮርፖሬሽንና የዊንጉ አፍሪካ ዳታ ማዕከል በትብብር እንዳዘጋጁት ታውቋል፡፡
የአይቲ ፓርክ ኮርፖሬሽኑን የሚያስተዳድረው የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትሩ ዶ/ር በለጠ ሞላ በጉባኤው መክፈቻ ላይ እንደገለጹት፤የኢትዮጵያን የዲጂታል ሽግግር እውን በማድረግ ረገድ አይቲ ፓርኩ ጉልህ ሚና የሚጫወት ይሆናል፡፡ ከዚህ አንጻር ጉባኤው ወቅታዊና ተገቢ መሆኑን ሚኒስትሩ አስምረውበታል፡፡
የአይቲ ፓርክ ኮርፖሬሽን ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ሔኖክ አህመድ በበኩላቸው በሰጡት ማብራሪያ፣ የኮርፖሬሽኑ ትልቁ ዓላማው ቢዝነስ መሥራት የሚያስችል ሥነምህዳር መፍጠር መሆኑን ጠቁመው፤ ለዚህም ሁሉም በጋራ የሚጠቀምበት ሪሶርስ በአንድ ቦታ ያቀርባል ብለዋል፡፡
ራዕያችን የአፍሪካ የአይቲ ማዕከል መሆን ነው ያሉት ዋና ሥራ አስፈጻሚው፤ ይህን ለማሳካትም የቴክኖሎጂ ሽግግርን በማምጣትና አቅምን በማሳደግ ዓለማቀፍ ተወዳዳሪነትን ማጎልበት እንደሚያስፈልግ አጽንኦት ሰጥተው ተናግረዋል፡፡
በዛሬው ጉባኤ ላይ በኢትዮጵያ የመጀመሪያውን የግል የዳታ ማዕከል፣ በአይቲ ፓርክ ገንብቶ አገልግሎት መስጠት መጀመሩን የጠቆመው ዊንጉ አፍሪካ የዳታ ማዕከል ኩባንያ፤ በምሥራቅ አፍሪካ ኢትዮጵያ፣ ጅቡቲ፣ ሶማሊላንድና ታንዛንያን ጨምሮ በአራት አገራት በዘርፉ አስተማማኝ አገልግሎት እየሰጠ የሚገኝ ስመ-ጥር ኩባንያ ነው ተብሏል፡፡
ኩባንያቸው በቀጣናው ተጠቃሽ የዳታ ማዕከል አገልግሎት አቅራቢ መሆኑን የገለጹት የዊንጉ አፍሪካ ዳታ ማዕከል ካንትሪ ዳይሬክተር አቶ ተሾመ፤ በኢትዮጵያም ዓለማቀፍ ደረጃውን የጠበቀ አስተማማኝ የዳታ ማዕከል መገንባቱን ጠቁመው፤ በዋናነት የፋይናንስ ዘርፉና የቴክኖሎጂ ተቋማት የአገልግሎቱ ተጠቃሚ እንደሚሆኑ ተናግረዋል፡፡
ዊንጉ አፍሪካ ወደ ኢትዮጵያ ገብቶ ሥራ ከጀመረ 18 ወራት ማስቆጠሩን የጠቆሙት ዳይሬክተሩ፤ የዚህ ጉባኤ አንዱ ዓላማ እነዚህ የፋይናንስና ቴክኖሎጂ ተቋማት ከፍተኛ ወጪ አውጥተው፣ የየራሳቸውን የዳታ ማዕከል ከመገንባት ይልቅ በኛ ማዕከል ቢጠቀሙ፣ የበለጠ እንደሚያዋጣቸው መረጃና ግንዛቤ ለመስጠት ነው ብለዋል፡፡ ጉባኤው አጋርነትና ትብብር የመፍጠሪያ መድረክ እንደሚሆንም ጨምረው አመልክተዋል፡፡
የዳታ ማዕከሉን ከሚመሩት ውስጥ 90 በመቶው ኢትዮጵያውያን መሆናቸው የገለጹት የኩባንያው አመራሮች፤ ማዕከሉ ለወጣት ኢትዮጵያውያን የቴክኖሎጂ ኢንጂነሮች ትልቅ የሥራ ዕድል መፍጠሩን አውስተዋል፡፡
የዘርፉ ዓለማቀፍ ተዋናዮች በአጋርነት አብረውን እንዲሰሩ መሳብ ችለናል ያሉት አመራሮቹ፤ የመንግሥት ደንብና መመሪያዎች ወጥተው እንደተጠናቀቁ እኒህ ተዋናዮች ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ ገልጸዋል፡፡ ማይክሮሶፍት፣ ቲክቶክና ሜታ (የቀድሞው ፌስቡክ) የመሳሰሉ ግዙፍ ዓለማቀፍ የቴክኖሎጂ ኩባንያዎች ወደዚህ አገር እንዲመጡም እየሰራን ነው ብለዋል - የዊንጉ አፍሪካ ዳታ ማዕከል ኩባንያ አመራሮች፡፡
የዊንጉ አፍሪካ ዳታ ማዕከል፣ በ50 ሚሊዮን ዶላር ወጪ መገንባቱ ይታወቃል፡፡
በዚህ ለግማሽ ቀን በሸራተን አዲስ በተካሄደው ጉባኤ ላይ፣ የአይቲ ኢንዱስትሪው መሪዎች፣ የመንግሥት ከፍተኛ ባለሥልጣናትና የፋይናንስ ተቋማት አመራሮች ተሳትፈዋል፡፡
የአምራች ኢንተርፕራይዞች አገር አቀፍ ኤግዚቢሽንና ባዛር ለ5 ቀናት ይካሄዳል
የአምራች ኢንተርፕራይዞች አገር አቀፍ ኤግዚቢሽንና ባዛር ለ5 ቀናት ይካሄዳል
• ኤግዚቢሽንና ባዛሩ ታህሳስ 3 በስካይ ላይት ሆቴል ይከፈታል
”ኢትዮጵያ ታምርት፤ እኛም እንሸምት” በሚል መሪ ቃል፣ ”የኛ ምርት” የተሰኘ የአምራች ኢንተርፕራይዞች አገር አቀፍ ኤግዚቢሽንና ባዛር፣ ከታሕሳስ 3 እስከ ታሕሳስ 7 ቀን 2016 ዓ.ም በስካይ ላይት ሆቴል እንደሚካሄድ ተገለጸ፡፡
የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት አመራሮችና የፕራና ኢቨንትስ ዳይሬክቲንግ ማናጀር፣ ኤግዚቢሽንና ባዛሩን አስመልክቶ ዛሬ ጠዋት ረፋዱ ላይ በስካይ ላይት ሆቴል ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል፡፡
”የኛ ምርት” የተሰኘው ኤግዚቢሽንና ባዛር ዋና ዓላማ፣ አምራች ኢንተርፕራይዞች በምርት ትውውቅ፣ በምርት ሽያጭ፣ በገበያ ትስስር፣ በቴክኖሎጂ ሽግግር፣ በልምድና የመረጃ ልውውጥ የተሻለ አቅም መፍጠርና የዘርፉን ፋይዳ ማሳየት የሚያስችላቸውን መድረክ መፍጠር ነው ተብሏል፡፡
በዚህ ኤግዚቢሽንና ባዛር፣ ከመላ አገሪቱ የተውጣጡ ከ100 በላይ የጨርቃጨርቅና አልባሳት ውጤት አምራቾች፣ የፕላስቲክ ውጤት አምራቾች፣ የቆዳና የቆዳ ውጤት አምራቾች፣ የአግሮ ፕሮሰሲንግ አምራቾች፣ የኬሚካል ውጤት አምራቾች፣ የማዕድንና ጌጣጌጥ ውጤት አምራቾች፣ የእንጨትና ብረታ ብረት ውጤት አምራቾችና ሌሎች ዋና ድጋፍ ሰጪ ተቋማት የሚሳተፉበት ሲሆን፤ ከ50ሺ በላይ ገዢና ጎብኚዎች ይስተናገዱበታል ተብሎ ይጠበቃል፡፡
ኤግዚቢሽንና ባዛሩ፣ ከመላው ኢትዮጵያ የተውጣጡ ውጤታማ የአገር ውስጥ አምራች ኢንተርፕራይዞች በአንድ ጣሪያ ሥር ተሰባስበው ከመላ አገራችን ከሚመጡ የህብረተሰብ ክፍሎችና ከአጋር ተቋማት ጋር የገበያ ትስስር ለመፍጠር የሚያስችል፣ ልምድና ተሞክሮ ለመጋራት ምቹ ዕድል የሚፈጥር እንዲሆን ለማስቻል ጥረት መደረጉ የተገለጸ ሲሆን፤ በተጨማሪም፣ አምራቾች የደረሱበትን የቴክኖሎጂና የምርት የእድገት ስኬት ደረጃ፣ ልምድና ተሞክሮ የሚያካፍሉበት እንዲሁም በዘርፉ ጥናት ያደረጉ ምሁራን ጥናታዊ ጽሁፍ የሚያቀርቡበትና የፓናል ውይይት የሚካሄድበት መድረክ እንደሚሆንም ለማወቅ ተችሏል፡፡
”የኛ ምርት” ኤግዚቢሽንና ባዛር፣ ዘላቂ የንግድ ትስስርን ለመፍጠርና የምርት ዕድገትን ለማረጋገጥ በሚያስችል መልኩ በጥንቃቄ የታቀደ ነው የተባለ ሲሆን፤ ለተሳታፊዎች የንግድና የምርት ስኬት የሚተጋ ከመሆኑም በላይ የአምራች ኢንተርፕራይዞች ምርቶችን ማህበረሰቡ በአገር ምርት እንዲኮራና ትኩረት ሰጥቶ እንዲሸምት ምቹ ሁኔታ የሚፈጥር ልዩ ኹነት መሆኑ ተጠቁሟል፡፡
”የኛ ምርት” የተሰኘውን አገር አቀፍ ኤግዚቢሽንና ባዛር፣ የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት እና ፕራና ኤቨንትስ በትብብር እንደሚያዘጋጁት ታውቋል፡፡
1242.pdf addisadmassnews
የቴአትር እና የቴሌቪዥን ፌስቲቫል እየተካሄደ ነዉ
አትሌት ታምራት ቶላ የኒው ዮርክ ማራቶን ውድድርን አሸነፈ
ረዳት ኮሚሽነር ደራርቱ ቱሉ ከጃፓን መንግስት ከፍተኛ የክብር ሽልማት ተበረከተላት
የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት ረዳት ኮሚሽነር ደራርቱ ቱሉ ከጃፓን መንግስት ለውጭ ሀገር ዜጎች የሚሰጠውን የሀገሪቱን ከፍተኛ የክብር ሽልማት ተበረከተላት።
ሽልማቱ የተበረከተላት በኢትዮጵያና ጃፓን መካከል ያለው የስፖርት ዲፕሎማሲ እንዲጠናከር ላደረገችው አስተዋጽኦ መሆኑም ተገልጿል።
አትሌት ደራርቱ የቀድሞ የጃፓን ጠቅላይ ሚኒስቴር ሺንዞ አቤ በፈረንጆቹ 2014 ኢትዮጵያን በጎበኙበት ወቅት ከኢትዮጵያውያን አትሌቶች ጋር እንዲወያዩ እድርጋ እንደነበር ተመላክቷል፡፡
በአውሮፓውያኑ 2019 ላይም ደራርቱ የጃፓን ስፖርት ኤጀንሲ ኮሚሽነር ከሆኑት ሱዙኪ ዳይቺን እና የቶኪዮ ኦሎምፒክ ሃላፊ ሃሺሞቶ ሴይኮ ጋር በመምከር የልምድ ልውውጥ ማድረጓ ተገልጿል፡፡
ለረዳት ኮሚሽነር ደራርቱ ቱሉ የተሰጠው ይህ እውቅናና ሽልማት እኤአ ከ1875 ጀምሮ ለውጭ ሃገር ዜጎች በጃፓን መንግስት የሚሰጥ አንጋፋ የክብር ሽልማት መሆኑን በኢትዮጵያ የጃፓን ኤምባሲ መረጃ አመልክቷል።
ይህ ሽልማት የውጭ ሀገር ዜጎች በጃፓን እና በሌሎች ሀገራት መካከል ያለውን ወዳጅነት ለማሳደግ ላበረከቱት አስተዋፅኦ የሚሰጥ ሲሆን፤ ረዳት ኮሚሽነር ደራርቱ ቱሉም ይህን ከፍተኛ የክብር ሽልማት በማገኝት የመጀመሪያዋ ኢትዮጵያዊት ሆናለች።