Administrator

Administrator

በአንድ በረሀ ውስጥ ሁለት ሰዎች በፈረስ ሆነው ሜዳውን አቋርጠው በመሄድ ላይ ሳሉ ይገናኛሉ። ከሁለቱ የአንደኛው ፈረስ አንካሳ ነው። ባለ አንካሳው ፈረስ በረሀውን አቋርጦ አለሙ አገር ለመድረስ ፈረሱ አላስተማመነውም። ስለዚህም እንደምንም ብሎ ደህነኛውን ፈረስ ከሌላው ሰውዬ ለመውሰድ መላ ይፈልግ ጀመር።
በመጨረሻም እንዲህ አለው፡-
“ወዳጄ ሆይ፤ ፈረሶቻችን ከእኛው ጋር ለብዙ ጊዜ የኖሩ በመሆናቸው ጨክነን በአለንጋ አንገርፋቸውምና ፈጥነው ለመሄድ ዳተኝነት ይሰማቸዋል። ስለዚህ እንቀያየርና እንደልብ እየገረፍናቸው በረሀውን ፈጥነን እናቋርጥ።”
ባለ ደህነኛው ፈረስም ይህን አግባብ ያልሆነ የብልጠት ጥያቄ በብልሃት ሲመልስ፤
“ጥያቄህ መልካም ነበር። ነገር ግን የእኔ ፈረስ እንዳንተ ፈረስ ዳተኝነት የለበትምና ማንም እንዲገርፈው አልፈቅድም። የአቅሙን ያህል፣ ባለው ፍጥነት በረሀውን እያቋረጠ በመሄዱ ፈረሴ አንዳችም አለንጋ ሊያርፍበት አይገባም፤ የጭካኔ ተግባርም ሊፈፀምበት ተገቢ አይደለም” አለው።
ባለ አንካሳው ፈረስ ዘዴው ባለመሥራቱ ተናዶ ጠብ ለመጫር ፈለገ። ስለዚህም፣
“እኔ ነኝ ጨካኝ? ለሁለታችንም ጥቅም ባሰብኩ ጨካኝ ትለኛለህ? በጭራሽ ጭንቅላት የሌለህ ደደብ ሰው ነህ!” ሲል ነገር ጀመረው።
አንድ ሁለት ሲሉ ወደ ድብድብ ተሸጋገሩ። ባለ አንካሳው ፈረስ ጡንቻው ፍርጥም ያለ ነበርና ባለ ደህነኛውን ፈረስ በትግል ጥሎ፣ ፈረሱን ነጥቆት፣ የሱን አንካሳ ፈረስ ጥሎለት እየጋለበ ሄደ።
በትግል የተሸነፈው ሰው ግን ተስፋ ሳይቆርጥ ከወደቀበት ተነስቶ አንካሳው ፈረስ ላይ ወጥቶ መንገድ እያቆራረጠ ከሚቀጥለው መንደር ቀድሞ ገብቶ ለዳኛ ከሰሰው። የሰው ፈረስ የወሰደው ሰው ከዚያ መንደር ሲደርስ በዳኛ ተያዘና ተጠየቀ።
“ፈረሱ የገዛ ራሴ ፈረስ ነው። ያሳደግሁት፣ አብሮኝ የኖረ ፈረሴ ነው። ይሄንንም ሰው እንኳን ፈረስ ልወስድበት ዓይኑንም አይቼው አላውቅ!” ሲል ፍርጥም ብሎ መለሰ።
ዳኛው ሽማግሌና አስተዋይ ሰው ናቸው። ነገሩ የጉልበት ስራ እንዳለበት ገብቷቸዋል። ሆኖም ለተሰራው ተንኮል ምንም ማስረጃ አልነበራቸውምና ብዙ ካሰቡ በኋላ አንድ ዘዴ ታያቸው።
“በሉ ሁለታችሁም ፊታችሁን ዞራችሁ ቁሙ”
ሰዎቹ እንደተባሉት አደረጉ።
ዳኛው በርኖሳቸውን አውልቀው የደህነኛውን ፈረስ ፊት ሸፈኑት። ከዚያም ሰዎቹ እንዲዞሩ አዘዙና ያንን የሰው ፈረስ የነጠቀ ጉልበተኛ ፊቱ ወደተሸፈነው ፈረስ እያሳዩ እንዲህ ሲሉ ጠየቁት፡-
“ለመሆኑ ይሄ ፈረስ የግራው ነው የቀኝ ዐይኑ የታወረው?”
 ያም ጉልበተኛ ሰው ድንገተኛ ጥያቄ ስለሆነበትና ካልመለሰም እንደሚጋለጥ በማሰብ፤ በአቦ-ሰጡኝ
“የቀኝ ዐይኑ ነው!” ሲል መለሰ።
ዳኛውም በርኖሱን ከፈረሱ ፊት ገልጠው፤
“ይገርማል! ፈረሱ ዕውር ይሁን አይሁን እንኳ ሳታውቅ ነው፣ የእኔ ፈረስ ነው የምትለው። ፈረሱ ሁለቱም ዐይኑ ደህና ነው። ካንተ ጋር የኖረ ፈረስ ቢሆን ኖሮ ጥያቄውን በተገቢ መልኩ በመለስህ ነበር። ሆኖም የሰው ገንዘብ ነውና ልታውቀው አልቻልክም”
በማለት ፈረሱ ለባለቤቱ እንዲመለስለት አደረጉ።

***
“መውደዱ ጠንቶ አድልዎ ዕውር እንዳያደርገን፣
ጥላቻው ከሮ ህሊና እንዳያሳጣን እንጠንቀቅ” ብሏል አንድ ያልታወቀ ደራሲ። በየትም ቦታ፣ በማናቸውም ጉዳይ ላይ ብልሃትና እውቀት ከሌለ ዳኝነት መስጠት ከባድ ኃላፊነት፣ ከባድ ሥራ ነው። የተጣሉ ልጆች የተጣሉ ባልና ሚስት ከማስታረቅ ጀምሮ ተፎካካሪ ባለሙያዎችን አወዳድሮ ፍርድ እስከመስጠት ድረስ ርቱዕ ዳኝነት የሚሻ ጉዳይ ነው።
ትክክለኛ ዳኝነት በግፍ የሰው ንብረት እንዳይጠፋ፣ እንዳይወሰድ፣ አይጥ በበላ ዳዋ እንዳይመታ፤ ጉልበተኛ ደካማውን እንዳያጠቃ፣ መብት እንዲከበር፣ መልካም የሰራ እንዲመሰገን እንዲነሳሳ፣ ክፉ የሰራ እንዲወቀስ አለመሥራቱን እንዲያውቅ ያደርጋል። ለዚህ ደግሞ ተገቢውን ዳኝነት ለመስጠት የሚችሉ አስተዋይ ብልህ ዳኞች ያስፈልጋሉ። በተለይ ሽልማት የሚሰጥበት ዳኝነት ሲሆን ደግሞ፣ ከማቴሪያል እሴቱም ይልቅ ስም (ስምም ቢሉ ሙያዊ ስም) አለበትና የሽማግሌ እርጋታና ስክነት ያላቸው መክረው ዘክረው፣ አውጥተው አውርደው፣ ግራ ቀኙን አይተው፣ ያለ አድልኦ፣ ያለ ወገናዊነት ፍርድ የሚሰጡ ሰዎች ያስፈልጉታል። ይህን ሳያሟሉ አንድም ያለዕውቀት አንድም በድፍረት አሊያም በንዝህላልነትና ያለብስለት ተነስተው የተጣላ እናስታርቅ የሚፎካከርን እንዳኝ፣ ብርቱና ሰነፉን እንለይ ቢሉ፣ “ለራሱ ያልተገረዘ የሰው ዐይን ይይዛል” የተባለው ዓይነት ይሆናል።
መልካም ዳኛ ተገኝቶ፣ ሚዛናዊ ዳኝነት እንዲኖር የማስፈለጉን ያህል ደግ ያደረገን የሚያበረታታ ማሕበረሰብ መኖሩ ዋና ነገር ነው። ከአያሌ አሉታዊ ነገሮች መካከል ጥቂት አዎንታዊ ፋይዳዎችን አንጥሮ አውጥቶ እነሱን ለማጉላት የሚሞክር ህብረተሰብ፣ ለነገ የወደፊት ገንቢ ጥርጊያ መንገድ እንዲኖር ከወዲሁ ተመክሮውን ያነቃል። ጨለማ ከከበባት ህይወት መካከል ጥቂት የብርሃን ፍንጣቂ ሲያገኝ፣ ለዚያች ሰፊ ቀዳዳ የሚያበጅ ህብረተሰብ፣ ራእዩ ግቡን እንዲመታ የተለያየ መንገድ ይከሰትለታል። የሀሳብ አማራጭ፣ የመኖር አማራጭ፣ የትግል አማራጭ ይኖረዋል። ስለ ዛሬ ጨለማ ሳይሆን ስለ ነገ ብሩህ ህይወት ለማለም የአእምሮ ጭጋግ አይጫነውም። “የሚገድል ጦር ተኝቶም ይወጋል” ይሏልና ከመሰረቱ ቀና የሆነ ዜጋ የሚበጀውን ከጧቱ ማየት የነገውን በልበ-ሙሉነት መቅረጽ ለሰው፣ በህይወቱ እያለ ዋጋውን መስጠት፣ ለመልካም ስራ ወቅታዊ ውዳሴን አለመንፈግ አሉታዊ ማህበረሰብ ከመሆን ያድነናል። በዚህ መንገድ ጀግና ይፈጠራል። ኮከብ ይበራል። ለሀገር ዐይን የሚሆኑ ሰዎች ይፈልቃሉ - ይበቅላሉ - ይፀድቃሉ።
ግልጽ፣ የተረጋጋና ዲሞክራሲያዊ ህብረተሰብ እንዲኖር ቀና ቀናውን እንጂ ክፉ ክፉውንና ጉድፍ ጉድፉን ብቻ የሚያይ መሪ፣ ድርጅት፣ ፓርቲ አይደለም እሚበጀው። ከትንሿም እንቅስቃሴ ውስጥ ቢሆን ደግ ደጓን የሚያይ እንጂ መጥፎ መጥፎውን እሚያይ፣ ክፉ ክፉውን እሚያወራ ሰው ወንዝ አያሻግርም። አገር አያለማም። ህዝብ አያሳድግም። በመርፌም የሚለቀም ቢሆን ከእኛ ውጪ ባለው ሰው ወይም ቡድን ላይ ደህና ደህናውን ነገር መርጦ ማየት ከብዙ ደባ፣ ከብዙ መጠላለፍ፣ ከብዙ መጠፋፋት፣ ከብዙ ውድቀት ያድናል። የልብ አንካሳ እመንገድ ሲያድር፣ የእግር አንካሳ እቤቱ ደርሶ ያድራል እንደሚባለው መሆኑ ነው። ምን ነግሬ ላሳስቀው ከማለት ምን አድርጌ ላስለቅሰው የሚል ሲበዛ አሉታዊነት (Negativism) ይንሰራፋል። የሚሾም የሚሸለም ከማየት፣ የሚዋረድ የሚነጠቅ ማየት ያረካል። አሉታዊነት ሲከፋ አብሮ ማደግ ቀርቶ አብሮ መኖር የማያስችል አለመተማመንን ይፈጥራል። መግባባትን ያጨልማል። መቻቻልን ያዳፍናል። ፖሊሲ መቅረጽ፣ የአፈፃፀም አቅም መገንባት፣ ሙስና ማጥፋት፣ ድህነት ቅነሳ ሁሉም ያለ አዎንታዊ ፍቃደ-ልቡና፣ ያአመስጋኝና ወሮታ-ከፋይ ህብረተሰብ (Merit-Giving Society) አንድ ጋት አይራመድም።
ክፉ ክፉውን የሚያይ ሹም፣ ጉድፍ ጉድፉን የሚለቅም ባለስልጣን ለራሱ ብዙ ነጥብ ይሰጣልና ውሎ አድሮ ሌላውን ሁሉ አኮስሶ እያየ፣ ካለ እኔ ማን አለ ማለቱ አይቀርም። ህብረተሰቡም የእሱን ክፉ ስለሚመኝና የእሱን ጎዶሎ ስለሚፈልግ እንቅፋት ሲደረድርለት፣ መቃብር ሲምስለት፣ ቀን ሲጠብቅለት ነው የሚኖረው። በአሉታዊ ህብረተሰብ ውስጥ ሹሙ ከዜጋው፣ ደንጊያው ከቅሉ እንደተጋጨ እንደተላተመ ነው የሚከርመው። በእንዲህ ያለው ጊዜ ሰላም ይጠፋል። ሠርቶ ማደር ያቅታል። “ማክቤዝ እንቅልፍን ገደላት” እንዲል ሼክስፒር፣ ሹሙ ሁሉ በግፉ፣ በሙስናው፣ በአድሎአዊነቱ፣ በማን-አለብኝነቱ… ምክንያት እንቅልፉን ያጣል። ውሎ አድሮም ከዚህ ቀደም እንደታዩት ሹማምንት እዚያው የውድቀት ጉድጓድ ውስጥ ይገባል። ማህበረሰቡም የእጁን አገኘ ይለዋል። ከወደቀውም ሆነ ከራሱ ለነገዬ ብሎ የሚያኖረውም የእርምት ስንቅ የለም። ለአዲስ ሹም አጨብጭቦ፣ ደሞ ነገ ጥምብ- እርኩሱን አውጥቶ አንቅሮ ይተፋዋል። “ዛሬ ፈጥሮ ነገ ቀብሮ” እንዳለው ነው ደራሲው።
ህብረተሰብ ለእድገት እንዲሰለፍ አሉታዊ ባህሪን ማስወገድ አለበት። አዎንታዊ አስተሳሰብን (Positivism) ማዳበር አለበት። መልካም የሰራን ለማበረታታት፣ ለላቀ ለመሸለም፣ ያለ አድልዎ ለመፍረድ፣ ከልብ ለመደገፍ፣ ከልብ ለመንቀፍ፣ ግልጽ ለመሆን ሁኔታዎች መመቻቸት አለባቸው። ከጽንፍ ወደ ጽንፍ ከመሄድ ይልቅ ሌላ አማካይና አማራጭ መንገድ ማየት ይገባል። ያለ ብሔረሰባዊ መንገድ የትም አልሄድም ብሎ ተከርሞ ድንገት የባነኑ እለት ብሔረሰብ ይውደም ወደማለት ከተሄደ አደገኛ ጽንፈኝነት ይሆናል።
ማንም ይሁን ማን ለረዥም መንገድ ከተነሳ ሆደ-ሰፊ መሆን አለበት። ለዚህም የተቻለው ጥረት ሁሉ ሊደረግ ይገባል። በተለይ ኃላፊዎች፣ ሹሞች፣ ባለአደራዎች፣ መሪዎች ጥብቅ አደራ የሚጣልባቸው ናቸው። አለበለዚያ ይህ ሳይኖራቸው በስሜታዊነትና በማን-አለብኝ ከተዋጡ፣ ለራሱ ያልዳነ ለአማቱ መድኃኒት ይቆርጣል እንደተባለው ይሆናልና ከወዲሁ እናስብበት።
ፋሲካውን በአዳዲስ ሃሳብ እንፈስክ!!
መልካም የትንሳኤ በዓል!!

የፍየል ዋጋ አይቀመስም - የበግ ቅናሽ አሳይቷል

የትንሳኤ በዓል የገበያ ዋጋ ከገና በዓል የገበያ ዋጋ አንፃር መጠነኛ መሻሻል ማሳየቱን ነጋዴዎችና ሸማቾች ተናገሩ፡፡ የአዲስ አድማስ ሪፖርተሮች በከተማዋ የተለያዩ አካባቢዎች የሚገኙ ትልልቅ የገበያ ቦታዎችን ከቃኙ በኋላ ባገኙት መረጃ ነው የበዓል ግባቶች የዋጋ ሁኔታ  መጠነኛ  መረጋጋት ማሳየቱን ማረጋገጥ የቻሉት።  ነጋዴዎችና ሸማቾች እንደገለፁት፤ ለገና በዓል ገበያ የ1 ኪሎ የሽንኩርት ዋጋ 150 ብር የነበረ ሲሆን ሰሞኑን አንድ ኪሎ ቀይ ሽንኩርት ከ55-60 ብር እየተሸጠ ይገኛል። ለገና 11 እና 12 ብር የነበረው የፈረንድ እንቁላል አሁን በዘጠኝና በ10 ብር እየተሸጠ ይገኛል። ምንም እንኳን በዓሉ ከመቃረቡ በፊት የፈረንጅ እንቁላል ሰባት ብር ከሀምሳ ሲሸጥ የቆየ ቢሆንም አሁን ከ9-10 ብር መሸጡ ከገናው በዓል የዋጋ ሁኔታ አንፃር የተሻለ መሆኑን ሸማቾች ገልፀዋል። በስድስት ኪሎ፣ በመገናኛው ሾላ፣ በሰሜን ማዘጋጃው ሾላ ገበያ፣ በሀይሌ ጋርመንትና በፈረንሳይ አካባቢ በሚገኙ ገበያዎች የተዘዋወሩት የአዲስ አድማስ ሪፖርተሮች ለመቃኘት እንደሞከሩት፣ የዓመት በዓል ፍጆታዎች ዋጋ ከቦታ ቦታ መጠነኛ ለውጥ እንዳለው ለመታዘብ ችለዋል፡፡
በ6 ኪሎ አትክልት ተራ ቀይ ሽንኩርት 60 ብር፣ ካሮት 80 ብር፣ ነጭ ሽንኩርት 360 ብር፣ ሎሚ በኪሎ 250 ብር፣ ድንች 40 ብር እየተሸጠ ሲሆን ፈረንሳይ አካባቢ ትልቁ የወላይታ ዶሮ ከ1 ሺህ 300 እስከ 1 ሺህ 700 ብር ድረስ ለገበያ ቀርቧል፡፡ 5 ሊትር ኦማር ዘይት 1 ሺህ 150 ብር እየተሸጠ ሲሆን የ100 ብር ጭማሪ አሳይቷል።
መጠነኛና አነስ ያሉ የፈረንጅ ዶሮዎች ከ1 ሺህ 100 ብር ጀምሮ እየተሸጡ ሲሆን፣ የዳቦ ዱቄት አንደኛ ደረጃው በኪሎ 1 መቶ ብር እየተሸጠ ሲሆን፤ አንደኛ ደረጃ የሸኖ ቅቤ ለጋው 900 ብር መካከለኛው 800 ብር እንዲሁም በሳሉ 690 ብር እየተሸጠ ይገኛል፡፡
በመገናኛው ሾላ የገበያ ቅኝታችን ደግሞ  አንድ ኪሎ ቀይ ሽንኩርት ከ40-70 ብር፣ ነጭ ሽንኩርት ከ350 እስከ 400 ባሮ ሽንኩርት በኪሎ 45 ብር እየተሸጠ ሲሆን፤ በተለይ ነጭ ሽንኩር በአዘቦት ቀናት ሲሸጥበት ከነበረው ዋጋ በጣም መወደዱን ሸማቾች ተናግረዋል።  በዚሁ በመገናኛ ሾላ ገበያ የሀበሻ ዶሮ ከ1 ሺህ 200 እስከ 1 ሺህ ሰባት መቶ ብር ሲሸጥ፣ የፈረንጅ ዶሮ ከ1 ሺህ 100 እስከ 1 ሺህ 600 ብር ድረስ እየተሸጠ መሆኑን ለማወቅ ተችሏል፡፡ መካከለኛ የፈረንጅ ዶሮ ከ800 እስከ 850 ብር እየተሸጠ መሆኑንም የሾላን ገበያ የቃኘው ሪፖርተራችን ገልጷል፡፡
በፈረንሳይ የበዓል ገበያም ሆነ በሾላ ገበያዎች  ዶሮ እዚያው ገዝቶ እዚያው የማሳረድ ባህል እየተስፋፋ ሲሆን ምንም እንኳን በቅኝታችን ወቀት ገና ፆሙ ያልተፈታ  ባለፈው ገና አንድ ዶሮ አርዶ ለመገንጠል ከ3-5 ደቂቃ እንደሚፈጅና ለአንድ ዶሮ 100 ብር ያስከፍሉ እንደነበር አረጋግጠናል፡፡ በሾላ ደግሞ ከ50 ብር እስከ 150 ብር ለዶሮ አራጅ እንደሚከፈል ሸማቾች ተናግረዋል፡፡
በሾላ ገበያ የሸኖ ቅቤ ለጋው በ950 ብር የሚሸጥ ቢሆንም ሲሆን፤ መካከለኛው 850 ብር፤በሳል ቅቤ በ750 ብር እየተሸጠ ነው። በበዓል ገበያ ቅኝታችን በሾላ ገበያ ካገኘነው የበዓል ግብአት ውስጥ ለጠላ የሚሆን የተመጣጠነ ውህድ ዱቄት (ጌሾ ብቅል፣ አሻሮ ተዘጋጅቶ የተቀላቀለ) ሲሆን፤ 1 ኪሎ ግራም የታሸገ የጠላ ምጥን 200ብር እንደሚሸጥ ለማወቅ ተችሏል፡፡ ከጠላ ምጥኑ ጎን ለጎን ደግሞ አልኮል የሌለውና ከገብስ ብቻ የሚዘጋጀው “ኬኔቶ” (መውደድ) ለሚባለው መጠጥ የሚውል አረር ተደርጎ የተቆላ ገብስ በ1 ኪሎ ግራም መጠን ታሽጎ እንዲሁ በ200 ብር እየተሸጠ ይገኛል፡፡
አዲስ አድማስ ሀይሌ ጋርመንት አካባቢ የሚገኘውን የበግና የፍየል ገበያ ለመቃኘትም ሞክሯል፡፡ በዚሁ ቅኝት ምንም እንኳን እንደቀድሞዎቹ የበዓላት ድባብ የደመቀና የደራ የገበያ እንቅስቃሴ ባናስተውልም፣ ነጋዴዎች ግን ከቀደሙት በዓላት የዋጋው ሁኔታ ጥሩ የሚባል መሆኑን ገልፀውልናል፡፡ ከገበያው በበዓሉ ዋዜማ እየደመቀ እንደሚሄድና የሸማቹ መጠን ይጨምራል የሚል ተስፋ እንዳላቸው ገልፀዋል፡፡
በዚሁ የቁም እንስሳት የግብዓት ስፍራ አነስ የሚል በግ ከ6 ሺህ ብር ጀምሮ እየተሸጠ ሲሆን መካከለኛ መጠን ያለው ከ8-10 ሺህ ሙክት በግ ከ12 እስከ 15 ሺህ ብር እየተጠራበት እንደሆነ ለማወቅ ተችሏል፡፡ የአሁኑ የበዓል ሰሞን የበግ ዋጋ ካለፈው ዓመትም ሆነ ካለፈው ገና የበግ ዋጋ አንፃር ቅናሽ እንዳለው ነው ነጋዴዎች የሚናገሩት አምና የመካከለኛ በግ ዋጋ 15 ሺህ ብር እንደነበር በማስታወስ፡፡
ዘንድሮ የፍየል ዋጋ ብቻ የሚቀመስ አይደለም የሚሉት ነጋዴዎ ትልቅና ሙክት የሚለው ፍየል እስከ 45 ሺህ ብር እየተጠራ እንደሆነ አብራርተዋል፡፡
በካራሎ የቁም ከብት እንስሰሳት ቅኝት ያደረጉት የአዲስ አድማስ ሪፖርተሮች በዚህ ገበያ የበሬ ዋጋ ምን ያህል ነው በማለት ነጋዴዎችን ገዢዎችን ያነጋገሩ ሲሆን ከ80 ሺህ እስከ 200 ሺህ ብር ባለው የዋጋ መጠን እንደየአይነታቸውና እንደየመጠናቸው እየተሸጡ ነው፡፡ አነስተኛ የሚባለውና ከጥጃ ከፍ ያለው ወይፈን 30 ሺህ ብር እየተባለ ነው፡፡
በሀገሪቱ የተለያዩ አካባቢዎች የተከሰተው የፀጥታ ችግር በሬ በግ፣ ዶሮና ፍየል እንደልብ ወደከተማ ለማምጣት አስቸጋሪ በመሆኑ ለገበያው መቀዛቀዝ አንዱ ምክንያት ሲሆን ከኑሮ ውድነቱ የተነሳ የሸማቹ የመግዛት አቅም በመዳከሙ ሌላው ለበዓል የገበያ ድባብ እንደምክንያት ተጠቅሷል በሸማቾችና በነጋዴዎች ከላይ የተጠናቀረው የገበያ ቅኝት ባለፈው ረቡዕና ጋዜጣው ማተሚያ ቤት እስከገባበት ሀሙስ ማታ ድረስ የተደረገ መሆኑን እየገለፅን ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች መልካም የትንሳኤ በዓል እንዲሆን እንመኛለን፡፡


በትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር አመራሮች መካከል፣ በፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት አፈፃፀም ዙሪያ፣ “ሰላም ፈላጊ እና ጦርነት ፈላጊ አለ” በሚል እየተፈጠረ ያለው የልዩነት ትርክት ስህተት ነው፤ ሲሉ የክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር  ምክትል ፕሬዚዳንት  ጄነራል ታደሰ ወረደ ተናገሩ፡፡
ጄነራሉ ባለፈው ረቡዕ ሚያዝያ 23 ቀን 2016 ዓ.ም  ለትግራይ ክልል መገናኛ ብዙኃን በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ፣ የፕሪቶሪያ ግጭትን በዘላቂነት የማቆም ስምምነት አተገባበርን በተመለከተ ጊዜያዊ አስተዳደሩ ከፌደራል መንግስትና ከመከላከያ ሠራዊት ጋር የሁለት ቀን ውይይት ማድረጉን አመልክተዋል።
የፕሪቶሪያ ውል አተገባበርን በተመለከተ  በተደረገው  ውይይት፣ የአፈፃፀም ስምምነት ላይ ተደርሷል ያሉት ምክትል ፕሬዚዳንቱ፤ “ከውይይቱ የማጠቃለያ ስምምነት በመነሳት የትግራይ ደቡባዊ ዞንና ፀለምት እስከ ግንቦት 30 ቀን 2016 ዓ.ም.፤ የምዕራብ ትግራይ ጉዳይ ደግሞ እስከ ሰኔ 30 ቀን 2016 ዓ.ም.  ዕልባት እንዲያገኙ የጋራ መግባባት ላይ ደርሰናል” ብለዋል።
ተፈናቃዮች በሁለት ወራት ውስጥ ወደቀያቸው  እንደሚመለሱ የገለጹት ጄነራል ወረደ፤ ተፈናቃዮቹ  ወደቀያቸው ከመመለሳቸው በፊት “መሬታቸው፣ ቤታቸውና እርሻቸው ተይዞ ስለሚገኝ በመጀመሪያ ምቹ ሁኔታ እንዲፈጠር” መግባባት  ላይ መደረሱን ጠቁመዋል፡፡
አያይዘውም፤ “ትጥቅ ማን ይፈታል ? እንዴትስ ይፈታል? የትኞቹ አስተዳደሮች ይፈርሳሉ? ተፈናቃዮች በምን መልኩ ይመለሳሉ?” በሚሉ ነጥቦች ላይ ውይይት ተካሂዶ ዝርዝር እቅድ እንደወጣለት ጠቅሰዋል።
 በትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር አመራሮች መካከል፣ በፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት አፈፃፀም ዙሪያ፣ “ሰላም ፈላጊ እና ጦርነት ፈላጊ አለ” በሚል እየተፈጠረ ያለው የልዩነት ትርክት ስህተት ነው  ያሉት ጄነራሉ፤ “ትርክቱ ስህተት መሆኑን ለፌደራል መንግሥት ገለፃ ሰጥተናል” ብለዋል፡፡ ይሁንና ጄነራሉ  እየተፈጠረ ነው  ያሉት የትርክት ስሕተት ከየትኛው ወገን እንደመነጨ በግልጽ አልተናገሩም፡፡
“የፕሪቶሪያው ውል ስምምነቱ ከተፈፀመበት ቀን ጀምሮ ከማንኛውም አይነት ግጭት በፀዳ መልኩ ተፈፃሚ ይሆናል ተብሎ ባይጠበቅም፣ አሁን መሬት ላይ ካለው ሁኔታ አንጻር  አንዳችም ለግጭት የሚጋብዝ ሁኔታ የለም” ያሉት  ጄነራሉ፤ “የፌደራል መንግስት በበኩሉ፣ የስምምነቱን ትግበራ እስከ ታች ድረስ እንደሚያወርደው እንጠብቃለን” ብለዋል፡፡  
ከሰሞኑ በራያ ወረዳዎች እና አላማጣ ከተማ እንደ አዲስ ከተቀሰቀሰው ግጭት ጋር ተያይዞ የተፈናቀሉ ሰዎች ቁጥር ከ50 ሺህ ማለፉን  የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የሰብዓዊ ጉዳዮች ማስተባበሪያ ጽህፈት ቤት (ኦቻ) አስታውቋል።

ሕብረት ባንክና ማስተር ካርድ የቅድመ ክፍያ ህብር ማስተር ካርድ አገልግሎትን አስተዋወቁ።
ሁለቱ ተቋማት ከትላንት በስቲያ ሀሙስ በህብረት ባንክ ዋና መስሪያ ቤት አዳራሽ ነው አገልግሎቱን በጋራ ያስተዋወቁት፡፡
ህብረት ባንክ ከማስተር ካርድ ጋር በመተባበር እውን ያደረገው ህብር የቅድመ ክፍያ ሕብር ማስተር ካርድ አገልግሎት ደህንነቱ የተጠበቀ፣ ኢትዮጵያዊያን በሌሎች የዓለም ሀገራት የሚኖራቸውን ግብይት ምቹ በሆነ ከባቢ እንዲያከናውኑ የሚያስችል፣ የፋይናንስ አካታችነትንና ዲጂታል ትራንስፎርሜሽንን ለማምጣት ትልቅ ሚና ያለው ዘመናዊ የባንክ አገልግሎት መሆኑን የህብረት ባንክ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ መላኩ ከበደ ተናግረዋል፡፡
ሥራ አስፈፃሚው አክለውም የቅድመ ክፍያ ሕብር ማስተር ካርድ አገልግሎት “ዱዋል ኢንተርፌስ” (Dual Interface) ያለው በመሆኑ ካርዱን ወደ ክፍያ ማሽኑ በማስገባት ወይም በማስጠጋት አገልግሎት በቀላሉ እንዲያገኙ ያደርጋል ያሉት ዋና ስራ አስፈፃሚው፤ ሕብረት ባንክ ለቴክኖሎጂና ለትብብር ሥራዎች ትኩረት እንደሚሰጥም አብራርተዋል። ዋና ሥራ አስፈፃሚው አክለውም፤ “በህብረት ባንክ ውስጥ አጋርነትና ቴክኖሎጂ የዕለት ተእለት ተግባራችን ብቻ ሳይሆኑ የባንካችንን ስኬት የሚያግዙ ናቸው፤ ይህ ይፋ የተደረገው የቅድመ ክፍያ ህብር ማስተር ካርድ አገልግሎትም የዚህ ማሳያና ባንኩ ለያዘው የዲጂታል ፋይናንሽያል አካታችነት ወሳኝ ምዕራፍ ነው” ሲሉ በአፅንኦት ገልፀዋል። የማስተር ካርድ የምስራቅ አፍሪካና የህንድ ውቅያኖስ ደሴቶች ሲኒየር ምክትል ፕሬዚዳንትና  ካንትሪ ማናጀር ሻህሪያር አሊ በበኩላቸው በአጋርነት መስራት እጅጉን አስፈላጊ መሆኑን ገልፀው፣ ከህብረት ባንክ ጋር በህብረት ማስተር ካርድ አገልግሎት የተደረገው ትብብር፣ በኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን በመላው አፍሪካ የፋይናንስ አካታችነትንና ዲጂታላይዜሽንን ዕውን ለማድረግ ያለንን ቁርጠኝነት ያሳያል ብለዋል፡፡ የካርድ አገልግሎቱ ከክፍያ አማራጭነት ባሻገርም፣ ኢትዮጵያዊያን በዓለም አቀፍ ገበያ በቀላሉና ደህንነቱ በተጠበቀ ሁኔታ መሳተፍ የሚያስችላቸው መሆኑንም ተናግረዋል፡፡
በማስተር ካርድ የአፍሪካ ፕሬዚደንት ማርክ ኤሊያት ደግሞ ትብብሩ በአህጉር ደረጃ በሚኖረው በጎ ተፅእኖ ላይ ተመርኩዘው እንደተናገሩት ከህብረት ባንክ ጋር በመተባበር ይፋ የተደረገው የቅድመ ክፍያ ህብር ማስተር ካርድ አገልግሎት፣ ማስተር ካርድ በአፍሪካ የሚያካሂደውን የኢኮኖሚ ትራንስፎርሜሽን ለማሳካት የሚያደርገውን ጥረት ማሳያ ነው ብለዋል፡፡  
ህብረት ባንክ በኢትዮጵያ ከሚገኙ ቀደምት የግል ባንኮች አንዱ ሲሆን ለደንበኞች ምቹና ቀልጣፋ የሆነ ዘመናዊ የባንክ አገልግሎት በመስጠትና ቴክኖሎጂዎችን በማስተዋወቅ የተመሰከረለት ባንክ መሆኑም ተነግሯል። በይፋ የተዋወቀው የቅድመ ክፍያ ህብር ማስተር ካርድ አገልግሎት፣ የባንኩ ደንበኞች ወደ ውጪ ሲሄዱ በቀላሉ የሚገበያዩበት በካርድ ላይ የሚሞላ የውጪ ገንዘብ ያለበት ዲጂታል ካርድ ሲሆን፤ በዋናነት ሶስት ጠቀሜታዎች አሉትም ተብሏል፡፡
አንደኛው በውጪ ሀገር ያሉ ሆቴሎችና ድርጅቶች ገንዘብ በካሽ መቀበል እያቆሙ መሆኑን ተከትሎ፣ ደንበኞች በውጪ ቆይታቸው በካርዱ ዲጂታል ግብይት እንዲፈፅሙ የሚያስችል ሲሆን፤ ሁለተኛው ጠቀሜታው በካሽ ለማግኘት የሚያስቸግረውን ዶላር በካርዳቸው ሞልተው በመያዝ ካሽ ከመያዝ ይድናሉ ተብሏል። ሶስተኛው ጠቀሜታም በካርዳቸው የሞሉት ገንዘብ በመጀመሪያው ጉዟቸው ባያልቅ የተረፈውን ለሌላ ጉዞ በማቆየት መገልገል ይችላሉም ተብሏል፡፡


የተባበሩት አረብ  ኤሚሬቶች ንብረት የሆነው “ዲፒ ወርልድ ኩባንያ” የሚያስተዳድረው የበርበራ ወደብ፣ የኢትዮጵያን 30 በመቶ ጭነት እንዲያስተናግድ የሶማሌላንድ ባለሥልጣናት ማቀዳቸው ተነገረ፡፡
በዚህም መሰረት የወደብ አጠቃቀምና የጉምሩክ ሥርዓቶችን የተመለከተ ስምምነት በኢትዮጵያና ሶማሌላንድ መካከል መፈረም እንዳለበት የተገለጸ ሲሆን፤ ስምምነቱ በሚቀጥሉት 60 ቀናት ተጠናቅቆ  ሊፈረም እንደሚችል የሶማሌላንድ የወደቦች አስተዳደር አስታውቋል፡፡
የአስተዳደሩ ዋና ዳይሬክተር ሰኢድ ሃሰን አብዱላሂ በሰጡት ማብራሪያ፤ “ኢትዮጵያ ጎረቤታችን ናት፤ አብረን  ቢዝነስ መሥራት እንፈልጋለን። በአሁኑ ወቅት የወደብ አጠቃቀም ስምምነት እያዘጋጀን ነው። አንዴ ስምምነቱን ከተፈራረምን በኋላ፣ በመጀመሪያው ዓመት ከኢትዮጵያ ጭነት 30 በመቶውን እናስተናግዳለን” ብለዋል።
ከጥቂት ወራት በፊት እ.ኤ.አ. ጥር 1 ቀን 2024 ዓ.ም ኢትዮጵያና ሶማሌላንድ የተፈራረሙት የመግባቢያ ስምምነት በተመሳሳይ ወደ ተግባር የሚገባበት የመጨረሻው ስምምነት በ2 ወራት ገደማ ውስጥ ይጠናቀቃል ተብሎ እንደሚጠበቅም  የሶማሌላንድ ባለሥልጣናት ጠቁመዋል፡፡
የመግባቢያ ስምምነቱ ከተፈረመ በኋላ ውይይቶች ሲደረጉ መቆየቱን ያመለከቱት  ባለሥልጣናቱ፤ የቴክኒክ ኮሚቴዎች መዋቀራቸውንም ተናግረዋል። የመግባቢያ ስምምነቱ  ከመጨረሻው ሂደት ላይ ደርሶ ወደ ተግባር ከተገባ ኢትዮጵያ በሶማሌላንድ የባህር ዳርቻ ላይ የጦር ሰፈር በሊዝ ኪራይ እንደምታገኝ የተገለጸ ሲሆን፤ ሶማሌላንድ በበኩሏ፣ ለረዥም ጊዜያት ስትፈልገው የነበረውን እንደ አገር ዕውቅና የማግኘት ዕድል እንደሚፈጥርላት ባለሥልጣናቱ አመልክተዋል።
ለንግድ ስራ ሌላ ወደብ መገንባት ሳያስፈልግ፣ የበርበራ ወደብን ኢትዮጵያ እንደምትጠቀምበት የሶማሌላንድ ባለሥልጣናት  መግለጻቸው  የተዘገበ ሲሆን፤ ከዚህ ቀደም ኢትዮጵያ፣ ዲፒ ወርልድ እና ሶማሌላንድ የበርበራ ወደብን በጋራ  ለማልማት ስምምነት መፈጸማቸው ይታወሳል።

አበዳሪ ተቋም በማጣት ለረጅም ጊዜ የተንገላቱ ደንበኞችን የብድር አቅርቦት በአጭር ጊዜ በማስተካከል ትላንት ሚያዝያ 25 ቀን 2016 ዓ.ም መኪኖችን አስረክቧል::

ካፒታል የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኃላፊነቱ የተወሰነ የህብረት ስራ ማህበር ከግዙፉ የመኪና ገጣጣሚ አክሎክ ሞተርሰ ጋር ባለው ስምምነት መሰረት ከጠቅላላ 1 ሺ 20 መኪኖች ውስጥ በመጀመሪያው ዙር 20 መኪኖችን ለተበዳሪዎች አቅርበዋል::  በቀጣይም ለበርካታ አባላቶቹ ብድር ለማቅረብ ዝግጅቱን አጠናቋል::

በትላንትናው ዕለት በፖሊስ ተይዘው የተወሰዱ ሁለት የማሕበረ ቅዱሳን አመራሮች በዛሬው ዕለት ከእስር ተፈተው ወደ ቤታቸው መመለሳቸው ተሰምቷል፡፡ አመራሮቹ  በፖሊስ የተያዙትና የተወሰዱት  ከመኖሪያ ቤታቸው እንደነበር ታውቋል፡፡

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስትያን፣ ሰንበት ትምሕርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ (ማሕበረ ቅዱሳን) ሰብሳቢ የሆኑት ሊቀ ትጉሃን ቀሲስ ዶክተር ሙሉጌታ ስዩም እና የማሕበረ ቅዱሳን ዋና ጸሐፊ መምህር ዋሲሁን በላይ፣ ትላንት በፖሊስ ተይዘው ሜክሲኮ ወደሚገኘው የፌደራል ፖሊስ የወንጀል ምርመራ ቢሮ መወሰዳቸውን ማሕበረ ቅዱሳን ቴሌቪዥን ዘግቦ ነበርለ፡፡  

የሁለቱ አመራሮች መኖሪያ ቤት በትላንትናው ዕለት በፖሊስ የተፈተሸ ሲሆን፤ አመራሮቹ ተይዘው የተወሰዱበት ምክንያት እስካሁን  አልታወቀም፡፡

በተያያዘ ዜና፣ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስትያን ቅዱስ ሲኖዶስ ጽሕፈት ቤት ጸሐፊ ሆነው ሲያገለግሉ የነበሩት ሊቀ ማእምራን ብርሃኑ ተክለያሬድ ባለፈው ሳምንት  ሐሙስ ከመኖሪያ ቤታቸው በፖሊስ ተይዘው መወሰዳቸው ተነግሯል።

ባለቤታቸው ወይዘሮ ኢየሩሳሌም ተስፋው በፌስቡክ ገጻቸው ላይ ባጋሩት መረጃ፤ መሪጌታ ብርሃኑ በቁጥጥር ስር የዋሉት ከማለዳው 12 ሰዓት ላይ ነበር፡፡ ሊቀ ማእምራን “ለጥያቄ እንፈልግዎታለን” ተብለው ወደ ፌደራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ቢሮ እንደተወሰዱ ነው ባለቤታቸው ባጋሩት መረጃ  የጠቆሙት፡፡

ሊቀ ማእምራን ብርሃኑ፣ ከሳምንታት በፊት በቋሚ ሲኖዶስ ፈቃድ፣ የደቡብ አፍሪካ አሕጉረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ ተደርገው መዘዋወራቸው ታውቋል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለ2016 ዓ.ም የትንሣኤ በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ያስተላለፉት መልዕክት ሙሉ ቃል እንደሚከተለው ቀርቧል:-

እንኳን ለ2016 ዓ.ም የትንሣኤ በዓል በሰላም አደረሳችሁ!

ኢየሱስ ክርስቶስ መከራና ሞት፤ ግፍና ሙስናን፤ ሲዖልና መቃብርን አሸንፎ የተነሣበትን የትንሣኤ በዓል በየዓመቱ እናከብራለን። ከበዓሉ በፊት የሕማማትን ሰሞን እናሳልፋለን። ሰሞነ ሕማማቱ ፈተናን፣ ስቃይን፣ ክህደትን፣ አሳልፎ መስጠትን፣ የክፉዎችን ኅብረት፣ የምናስብበት ነው። ሐሰት ያሸነፈች፣ እውነት የተሸነፈች መስላ የታየችበት ነው። ብዙዎች መሥዋዕትነትን ፈርተው የሸሹበት ነው። አንዳንዶችን የሚያልፍ ጎርፍ ወሰዳቸው፤ አንዳንዶችን የሚሰክን ማዕበል ነጠቃቸው። ጥቂቶች ከሕማማቱ አልፈው ትንሣኤውን ለመመልከት ቻሉ።

የከተማው ጩኸት እና የሐሰቱ ወሬ እንኳን በሩቅ የነበሩትን፣ ቅርብ የነበሩትንም አሸንፏቸዋል። የሆሳዕና ዕለት ደግፈው የወጡት ከሦስት ቀን በኋላ ሊቃወሙ ሲወጡ ምንም አልመሰላቸውም። ድጋፋቸውም ተቃውሟቸውም ሁለቱም የጥቅም እንጂ የመርሕ አልነበረም። ሁለቱም ከእውነታው የተጣሉ ነበሩ። ሕማማት የውስጥና የውጭ ጠላቶች ተባብረውበታል። በሌላ ጊዜ ለሞት የሚፈላለጉ አካላት እውነትን ለመስቀል ሲሉ ግን ተባብረው ቆመዋል።

ሰዎቹ ያልተረዱት አንድ እውነታ ነበር። ከሕማማቱ ይልቅ ትንሣኤው ይበልጣል፤ ይረዝማልም። ሕማማቱ አምስት ቀን ሲሆን ትንሣኤው ግን አስር እጥፍ ይሆናል። የአምስት ቀን ፈተና የሃምሳ ቀን ዋጋ አለው። በርግጥ የሕማማቱን ሽብርና ዋይታ፣ መከራና እንግልት ለተመለከተ ትንሣኤ የሚመጣ አይመስለውም። ትንሣኤው ግን የታመነና የተረጋገጠ ነው። የበለጠ ማረጋገጥ የሚቻለውም ጸንቶ እንደ ዮሐንስ በመቆም ብቻ ነው።

ኢትዮጵያ በፈተና ውስጥ እያለፈች ነው። በፈተና ውስጥ የቆመች ሀገር ግን አይደለችም። በፈተና ውስጥ እያለፈች ያለች እንጂ። ወቅቱ ለኢትዮጵያ የሕማማት ሰሞን ይሆን ይሆናል። አራት ነገሮች ግን እውነት ናቸው። የመጀመሪያው የኢትዮጵያ ሕማማት አጭር መሆኑ፤ ሁለተኛው አጭር ቢሆንም ከባድ መሆኑ፤ ሦስተኛው ኢትዮጵያ ሕማማቱን ለማለፍ የሚያስችል ኃይል ያላት መሆኑ፤ አራተኛው ከአጭሩ ሕማማት በኋላ ረዥሙ የኢትዮጵያ ትንሣኤ የሚመጣ መሆኑ ነው።

የተነሣነው ኢትዮጵያ እንደምትፈተን ዐውቀንም፤ አምነንም ነው። ለዘመናት የኖሩ ስብራቶችንና ብልሽቶችን ልናክም ስንነሣ መንገዱ አልጋ በአልጋ አይሆንም። ከችግሩ ማትረፍ የለመዱ አካላት ዝም አይሉም፤ ኢትዮጵያ በማሽን እንደሚረዳ ሕመምተኛ ሆና በሞትና በሕይወት መካከል እንድትኖር የሚፈልጉ ኃይሎች ዐርፈው አይቀመጡም።

ግን ሕማማቱን እኛ ካልተቀበልንላት ለኢትዮጵያ ማን ይቀበልላታል የመከራውን ቀንበር ካልተሸከምንላት የሀገር ልጅነቱ የቱ ጋ ነው “ኢትዮጵያ ኢትዮጵያ” እያሉ በስሟ ሲምሉ የነበሩ ብዙዎች ነበሩ፤ ከልባቸው ለቃላቸው ታምነው ልጅ የሆኗት ግን ጥቂቶች ብቻ ናቸው። አንዳንዶች በስሟ የሚገዘቱት እንጀራዋን ለመብላት እንጂ መከራዋን ለመካፈል አይደለም፤ በተቃራኒው እንጀራዋን በልተው ተረከዛቸውን አነሡባት።

የሕማማቱ ወቅት አጭር ቢሆንም ከባድ መሆኑን እናውቃለን። የኮሶ መድኃኒት እንዲያሽር ከተፈለገ በአንድ ጊዜ በከባዱ መወሰድ አለበት። በትንሽ በትንሹ ከተወሰደ አያሽርም። የኢትዮጵያም ሕማማት እንደዚሁ ነው።

በፊስካል ፖሊሲ፣ በግብርና፣ በማኑፋክቸሪንግ፣ በውጭ ጉዳይ ፖሊሲ፣ በኅብረ ብሔራዊ አንድነት፣ ነጻነትን በማስተዳደር፣ በክልል አደረጃጀት፣ በሲቪል ሰርቪስ፣ በጋራ ትርክት ግንባታ፣ ወዘተ. የተረከብናቸው ውዝፍ ዕዳዎች ብዙ ናቸው። ወገባችንን አሥረን፣ እጅጌያችንን ሰብስበን መራራውን የኮሶ መድኃኒት ውጠን፣ እነዚህን ችግሮች ካልፈታናቸው ቆመው አይጠብቁንም። በፈጣኑ ዓለም ውስጥ ቀስ ብለን ልንሄድ አንችልም። ተጠንቅቀን ግን ፈጥነን፤ አስበን ግን ዋጋ ከፍለን መጓዝ አለብን። ይሄ ነው ሕማማቱን የሚያሳጥረው።

ኢትዮጵያ ሕማማቱን ለማለፍ የሚያስችል ኃይል አላት። ከዚህ በፊትም ብዙ አልፋለች፣ አሳልፋለች። የማይተዋት አምላክ አላት። የሚወዳት፣ የሚያስብላት ብቻ ሳይሆን የሚሞትላትም አመራር አላት። ዓላማ አይቶ ዋጋ የሚከፍል ሕዝብ አላት። አንጡራ ሀብት አላት። ይሄ የፈጣሪ፣ የአመራሩ፣ የሕዝቡ እና የአንጡራ ሀብቷ አራት ማዕዘናዊ ዐቅም፣ ሕማማቱን ማሳጠርና ማስቻል ብቻ ሳይሆን ቀጥሎ የሚመጣውን ፋሲካ ረዥም እንዲሆን ያደርገዋል።

ብርቱውን ይዘናል – እንበረታለን፤ ኃይል በሚሰጠው እንታመናለን። ንጽሕናንና ለሀገር ያለንን በጎ ራእይ መሠረት አድገን ቆርጠን እንሠራለን። የጥብርያዶስ ሞቅታም ሆነ የፕራይቶሪዮን ግቢ ጩኸት ከመንገዳችን አያቆሙንም።

የሆሳዕና ድጋፍም ሆነ የዕለተ ዓርብ ተቃውሞ መንገዳችንን አያስቀይሩንም። የኢትዮጵያን እውነት ብቻ ተከትለን እንገሠግሣለን። በዚህም ሕማማቱን አሳጥረን የኢትዮጵያን የትንሣኤ ጊዜ እናረዝመዋለን።

በድጋሜ መልካም የትንሣኤ በዓል!

ኢትዮጵያ በልጆቿ ጥረት ታፍራና ተከብራ ለዘላለም ትኑር!!

ፈጣሪ ኢትዮጵያና ሕዝቦቿን ይባርክ!

በአሁኑ ሰዓት በአሜሪካ እየተካሄደ በሚገኘው የዓለም ሮቦቲክስ ሻምፒዮን ላይ ኢትዮጵያውያን ተማሪዎች እየተሳተፉ እንደሚገኙ ለማወቅ ተችሏል።

ለዚህ የዓለም ሮቦቲክስ ሻምፒዮን ኢትዮጵያውያን ተማሪዎችን ይዘው ወደ አሜሪካ የተጓዙት የኢትዮ ሮቦ ሮቦቲክስ የትምህርትና ውድድር ማዕከል መሥራችና ዋና ሃላፊ አቶ ሰናይክሪም መኮንን ናቸው።

በአሜሪካው ውድድር ላይ ለመሳተፍ የተመረጡት ተማሪዎች በቅርቡ እዚህ አዲስ አበባ በኢሊሌ ሆቴል በተካሄደ የአፍሪካ ሮቦቲክስ ሻምፒዮና የላቀ ውጤት ያመጡ ሲሆን፤ በቪዛ መዘግየትና በቲክኒካል ጉዳዮች  ከጉዞው የቀሩም ተማሪዎች እንዳሉ ታውቋል።

NEW YORK (AP) — Officers took protesters into custody late Tuesday after Columbia University called in police to end the pro-Palestinian occupation on the New York campus.

The scene unfolded shortly after 9 p.m. as police, wearing helmets and carrying zip ties and riot shields, massed at the Ivy League university’s entrance. Officers breached Hamilton Hall, an administration building on campus, to clear out the structure.

The demonstrators had occupied Hamilton Hall more than 12 hours earlier, spreading their reach from an encampment elsewhere on the grounds that’s been there for nearly two weeks.

A statement released by a Columbia spokesperson late Tuesday said officers arrived on campus after the university requested help. The move came hours after NYPD brass said officers wouldn’t enter Columbia’s campus without the college administration’s request or an imminent emergency.

Hamilton Hall
“After the University learned overnight that Hamilton Hall had been occupied, vandalized, and blockaded, we were left with no choice,” the school’s statement said, adding that school public safety personnel were forced out of the building and one facilities worker was “threatened.”

“The decision to reach out to the NYPD was in response to the actions of the protesters, not the cause they are championing. We have made it clear that the life of campus cannot be endlessly interrupted by protesters who violate the rules and the law.”

Columbia’s protests earlier this month kicked off demonstrations that now span from California to Massachusetts. As May commencement ceremonies near, administrators face added pressure to clear protesters.

More than 1,000 protesters have been arrested over the last two weeks on campuses in states including Texas, Utah, Virginia, North Carolina, New Mexico, Connecticut, Louisiana, California and New Jersey, some after confrontations with police in riot gear.

In a letter to senior NYPD officials, Columbia President Minouche Shafik said it was making the request that police remove protesters from the occupied building and a nearby tent encampment “with the utmost regret.” She also asked that officers remain on campus through May 17, which is after the end of the university’s commencement celebrations.

“Walk away from this situation now and continue your advocacy through other means,” New York City Mayor Eric Adams advised the Columbia protesters on Tuesday afternoon before the police arrived. “This must end now.”

The White House earlier Tuesday condemned the standoffs at Columbia and California State Polytechnic University, Humboldt, where protesters had occupied two buildings until officers with batons intervened overnight and arrested 25 people. Officials estimated the northern California campus’ total damage to be upwards of $1 million.

Page 1 of 705