Administrator

Administrator

ኤርትራ ራሷን እያወደመች ነው የኢትዮጵያ ትምህርት ችግሮች ቋንቋና ያለ እቅደ መስፋፋት ናቸው

            ፕሮፌሰር ተከስተ ነጋሽ በስዊድን አገር በኡፕስላ ዩኒቨርሲቲ የዘመናዊ ታሪክ ፕሮፌሰር ናቸው፡፡ ፕሮፌሰሩ በኢትዮጵያ ትምህርት ላይ ከፍተኛ ምርምሮችን ያደረጉ፣ በመስኩም የታወቁ ምሁር ሲሆኑ ከከዓምናው ጀምሮ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የታሪክ ትምህርት ክፍል ተጋባዥ ፕሮፌሰር ሆነው በማገልገል ላይ ይገኛሉ፡፡ እ.ኤ.አ በ1947 በአስመራ ከተማ ተወልደው የአንደኛ ደረጃ ትምህርታቸውን በአስመራ፣ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን በጅማ ተከታትለዋል፡፡ የመጀመሪያ ድግሪያቸውን ከአስመራ ዩኒቨርሲቲ በህግ አግኝተዋል፡፡ ከ1972 እስከ 1974 በአስመራ ዩኒቨርሲቲ ያስተማሩት ፕሮፌሰር ተከስተ፤ በለንደን ዩኒቨርሰቲ ከ“ስኩል ኦፍ ኦሪየንታል ኤንድ አፍሪካ ስተዲስ” ማስተርስ ድግሪ ያላቸውን ያገኙ ሲሆን ዶክትሬታቸውን ከስዊድን አገር ኡፕስላ ዩኒቨርስቲ በታሪክ ትምህርት ሰርተዋል፡፡ የኤርትራን ወቅታዊ ሁኔታ እንዴት ይገልፁታል? እኔ የኤርትራን ጉዳይ መከታተል ካቆምኩ አስራ ሶስት አመት ሊሆነኝ ነው፡፡ ምክንያቱም ልለው የምችለውን ሁሉ ብያለሁ፡፡

“Brothers at war” በሚል ከአንድ የኖርዌይ ተወላጅ ጋር በመሆን በፃፍነው መጽሐፍ፤ የኢትዮጵያና የኤርትራ ጦርትነት የወንድማማችነት ጦርነት ነው፤ ችግሩን ለመፍታት ሁለቱ አገሮች ወንድማማችነታቸውን ማመን አለባቸው ብለን ደምድመናል፡፡ ከዛ በኋላ ምንም ሠላም አልተገኘም፤ በኔ አስተያየት የሚገኝም አይመስለኝም፡፡ እስከአሁን በኢትዮጵያም ሆነ በኤርትራ ወንድማማችነቱን ማመን ላይ አልተደረሰም፡፡ የሁለቱ አገራት የወደፊት ግንኙነት ምን የሚሆን ይመስልዎታል? የኤርትራን ጉዳይ ማጥናት የተውኩት ተገድጄ አይደለም፡፡ በአንድ በኩል በኢትዮጵያ እየተካሄዱ ያሉ ነገሮች በጣም በጎ ናቸው፡፡ ኢትዮጵያ ብዙ ለውጥ እየተካሄደ ነው የሚል አቋም ስላለኝ ሲሆን በሌላ በኩል የኤርትራ ጉዳይ አልቆለታል ብዬ ስላመንኩ ነው፡፡ የጊዜ ጉዳይ ነው እንጂ ኤርትራ ራሷን በራሷ እያወደመች ነው፡፡ ኤርትራ ምንም ተስፋ የላትም ብዬ አምናለሁ፡፡

ወደ ጥያቄሽ ስመለስ… የኤርትራና የኢትዮጵያ ሁኔታ እንዴት ይቀጥላል ለሚለው በኔ አስተያየት ከዚህ በኋላ ጦርነት አይካሄድም። ኤርትራ ግን የሶማሊያን አይነት የምትሆንበት፣ በአንድ ልትመራ ወደማትችልበት ደረጃ ልትደርስ ትችላለች ብዬ አምናለሁ፡፡ ከኢሳያስ አፈወርቂ በኋላ ኤርትራ ሶማሊያን ትሆናለች በሚል የሚሰጡ አስተያየቶችን ይቀበላሉ ማለት ነው? አዎ፡፡ ኢሳያስ እስካለ እሱ የፈጠረው ስርዓት ይቀጥላል፡፡

የአለም አቀፉ ማህበረሰብ አቋም እና የኢትዮጵያ መንግስት የያዙት አቋምም ለዚህ አስተዋጽኦ ያደርጋሉ፡፡ ከኢሳያስ በኋላ ግን የኢኮኖሚ ችግር ብቻ ሳይሆን የብሔር ግጭቶች አሉ፡፡ ቆላማው የኤርትራ ክፍል የራሱ አጀንዳ አለው፤ ደገኞቹ ደግሞ እርስበርሳቸው በጣም የተከፋፈሉ ናቸው፡፡ ይህን መያዝ የሚችለው ኢሳያስ ብቻ ነው፡፡ ከሱ በኋላ አገሪቱን አንድ አድርጐ ወደፊት ሊያራምድ የሚቻል ይመጣል ብዬ አላምንም፡፡ የኤርትራ ጥያቄ ለምርጫ በቀረበበት ወቅት ከነበሩ አማራጮች ዋነኞቹ፤ መገንጠል፣ በፌዴሬሽን መቆየት እና አንድነት የሚሉ ነበሩ፡፡ በውድም ይሁን በግድ ሁሉም አማራጮች ተግባራዊ ሆነዋል፡፡ ኤርትራ ከተገነጠለች 23 አመት ሊሆናት ነው፡፡ በአሁኑ ወቅት አንድነት የሚለው አቋም ቅሪት አለ ወይስ ሙሉ በሙሉ ተሸርሽሯል? የደጋው ኤርትራ ባህል በመሠረቱ ኢትዮጵያዊነቱን እንደያዘ ነው፡፡ ኢሳያስ ስልጣን እንደያዘ በሶስተኛ አመቱ ሆላንድ መጥቶ ባደረገው ውይይት፤ እኔም እድሉን አግኝቼ ሰምቼዋለሁ፡፡ እኛ ሠላሳ አመት ሙሉ ታግለን ብዙ ሰው ሞቶብን፣ ባለፉት ሁለት አመታት ውስጥ የኤርትራ ህዝብ የከፈልነውን መስዋዕትነት ረስቶ ከኢትዮጵያ ጋር ወዲያ ወዲህ ይላል ብሎ ተናገረ፡፡ ኤርትራ ነፃ ከወጣች ጊዜ ጀምሮ እስከ ጦርነቱ ድረስ የኤርትራ ህዝብ ከኢትዮጵያ ተለይተናል የሚል ብዙ ስሜት አልነበረውም፡፡ ደርግ መሸነፉ ላይ ነበር እንጂ ከኢትዮጵያ ጋር የመለየቱ ብዙ ግንዛቤ አልነበረውም፡፡ ጦርነቱ ሲጀመር ስሜቱ መቀዛቀዙን መናገር ይችላል፡፡

ሌላው በደጋው ኤርትራ ያለው ትግርኛ ተናጋሪ ከጣሊያን ጊዜ የጀመረ የገዢና የተገዢ ግንኙነት ነበረው፡፡ እኛን ጣልያን ነው የገዛን በሚል፣ ትግራይ ያሉትን ትግሪኛ ተናጋሪዎች “እናንተ ከአዲግራት፣ ከመቀሌ፣ ከአድዋ የምትመጡ…” የሚል ነገር ነበር፡፡ ከጦርነቱ በኋላ የትግራይ ህዝብ የራሱን ማንነት ኢኮኖሚ በማሻሻል ላይ ስለሚገኝ በነዚህ ሁለት ትግሪኛ ተናጋሪዎች መካከል ያለው ፉክክር ማን ትግሬን ይወክላል የሚል ነው፡፡ ይህ ለጊዜው ችግር ሊፈጥር ይችላል፤ ግን እኔ እስከምረዳው ድረስ ኢትዮጵያዊነት ስሜት፣ ባህል፣ አስተሳሰብ አለ የምንል ከሆነ በደጋማው ኤርትራ አሁንም አለ። ከዛ ደግሞ ከአፋር ጋር ያለውን ትስስር ማየት ይቻላል፡፡ በኤርትራ ያሉ ቢለኖች አገዎች እንደሆኑ አይጠራጠሩም፤ አሁን ባለው ሁኔታ ምንም ማድረግ አይችሉም፡፡ ኩናማዎችንም ካየሽ ተመሳሳይ ነው፡፡ ወቅታዊውን የአፍሪካ ቀንድ ሁኔታ እንዴት ይገልፁታል? በአፍሪካ ቀንድ የኢትዮጵያ ሚና ከፍተኛ ነው፡፡ ሶማሊያ እና ኢትዮጵያን ካየን፣ ለሁለቱም የሚጠቅማቸው የሶማሊያ አንድ መሆን ነው፡፡ አሁን ያለው ሁለት ሶማሊያ በኔ አስተያየት ረጅም የሚጓዝ አይደለም፡፡ ከጥቅም አንፃር ካየነውም፣ ለኢትዮጵያም ሆነ ለሶማሊያ አይጠቅምም፡፡ በኤርትራና በኢትዮጵያ በኩል ስናየው፣ ኤርትራ የምትፈልገው ድንበር ሊኖር አይችልም፡፡ ይህን ደግሞ ሁለቱም አገሮች ያውቁታል፡፡

የኤርትራ ሁኔታ ከኢሳያስ በኋላ አዲስ መልክ ይይዛል፡፡ በአዲሱ ሁኔታ የኢትዮጵያ ሚና ምን ሊሆን እንደሚችል በሚገባ ማጤን ያስፈልጋል፡፡ የኢትዮጵያ የውጪ ጉዳይ ፖሊሲ የኢትዮጵያን ጥቅም ለመጪው ሁለት መቶ ሶስት መቶ አመት ሊያራምድ የሚችል ሆኖ መቀረፅ ይገባዋል፡፡ የኢትዮጵያን የፌደራል አወቃቀር እንዴት ያዩታል? አወቃቀሩ በፌደራል መሆኑ ጥሩ ነው፡፡ በብሔር መሆኑ ግን መጥፎ ነው፡፡ የኢህአዴግ መንግስት ያደረገው ትልቁ ስህተት ነው፡፡ ፌደራል ስርአት በፊትም የነበረ ነው፡፡ የኢትዮጵያን የኋላ ታሪክ ካየሽ የፌደራል አወቃቀር አዲስ አይደለም፡፡ ንጉሠ ነገስት ስንል እኮ ንጉሶች አሉ፡፡ ከበላያቸው ንጉሠነገስት አለ ማለት ነው፡፡ አካባቢያዊ ፌደራሊዝም ነበር፡፡ የኤርትራ ህዝብ አሁን ያሉበትን የነፃነት ሁኔታ ከቀድሞው ጋር ሲያስተያዩት ምን ትርጉም ይሰጥዎታል? እኔ እኮ በመጀመሪያም ኤርትራውያኖች ከማን ነው የሚገነጠሉት የሚል አቋም ነው ያለኝ። ማነው ከማን የሚገነጠለው? የደቡብ ወይም የኦሮሞ ህዝቦች እንገነጠላለን ቢሉ ኖሮ ምክንያት ነበራቸው፡፡ የኤርትራ የነፃነት ጥያቄ በተነሳበት ወቅት ኤርትራውያኑና ከላይ የጠቀስኳቸው ህዝቦች በኢትዮጵያ ውስጥ ያገኙትን እድል (Comparative advantage) ስናይ፣ ኤርትራውያኑ በጣም ተጠቃሚ ነበሩ፡፡ (በጣሊያን፣ በእንግሊዝ፣ በፌዴሬሽኑ ዘመን) በ1960ዎቹ የአዲስ አበባ ሀብታሞቹ እነሱ ነበሩ። በትምህርት መስክ ሃያ አምስት በመቶ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ ተማሪዎች ኤርትራውያን ነበሩ። የሁለተኛ ደረጃ ተማሪዎችንም ካየሽ 25 በመቶ የሚሆኑት ኤርትራውያን ነበሩ፡፡ ከተማረው ሰላሳ አምስት በመቶው ክፍል ኤርትራውያን ነበሩ፡፡

ይህን እድል ያገኙ ሰዎች ከኢትዮጵያ እንገነጠላለን ሲሉ ምክንያቱን ለማግኘት አስቸጋሪ ነው፡፡ ምንም ምክንያት አልነበራቸው፡፡ ለነፃነት የተደረገው እንቅስቃሴ 30 አመት ቢፈጅም ስልሳ ሺህ ሰው ቢሞትም በቂ ምክንያት አልነበረውም። የኔ ጥናት የጣልያን ቅኝ አገዛዝ በኤርትራ የሚል ነው። እንዲገባኝ ሞክሬያለሁ፡፡ ኤርትራ ከኢትዮጵያ መገንጠል እንዳለበት የሚያሳይ ምንም ነጥብ አላገኘሁም፡፡ ነፃ ወጣን አሉ፡፡ ሁለት አመት ሳይቆዩ እኛ የታገልነው ለነፃነት ብቻ አይደለም፤ የኛ ዕድል ከኢትዮጵያ ጋር ነው ማለት ጀመሩ፡፡ ይህን የሚሉት ተገደው ነው፤ ምክንያቱም የኤርትራ ኢኮኖሚ ከኢትዮጵያ ተገንጥሎ በራሱ ሊቆም የሚችል አይደለም፡፡ ኢትዮጵያ ልዩ አገር ነች፤ ነፃነቷን ጠብቃ የቆየች አገር ናት፡፡ የኤርትራ ቴሌቪዥን በቅርቡ “Ancient Eritreans” (የጥንት ኤርትራውያን) የሚል ዶክመንተሪ አቅርቦ ነበር፡፡ አይተውታል? (ረጅም ሳቅ) አላየሁትም፡፡ ግን ምንም አዲስ ነገር አይፈጥርም፡፡ ወጣቶቹ ኢትዮጵያን አያውቋትም፤ ነገር ግን መንግስት የሚያደርገው አንድ ነገር ነው፣ ህዝቡ የሚያስበው ሌላ ነገር ነው፡፡

መንግስት በቴሌቪዥን የሚየሳየውና ህዝቡ የሚመኘውና የሚያስበው ሌላ ነው፡፡ እስከቅርብ ጊዜ የኤርትራ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ከኢትዮጵያ ብትለያይም በድብቅ ወጣቶቻቸውን ለትምህርት ወደ ቤጌምድር (ጐንደር) ይልኩ ነበር፡፡ የኢሳያስን መረጃ በማየት ድምዳሜ ላይ መድረስ አይቻልም፡፡ ኤርትራዊውን ማን አገኘው፡፡ የተለየን ነን የሚል አቋም የት ነው ያለው? በኤርትራ የኢትዮጵያዊነት ስሜት ምን ያህል አለ ለሚለው መልስ ለማግኘት ድንበሩ መፍረስ አለበት፡፡ ለሁለቱ ህዝቦች መፍትሔ የሚሆነው በኤርትራ በኩል እየተጠየቀ ያለው ድንበር ሲሰመር ሳይሆን ከደርግ ሽንፈት በኋላ የተሰመረው መስመር ሲፈርስ ነው፡፡ ትናንት በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ቋንቋ፣ እውቀት እና የጋራ ህልውና በሚል የውይይት መነሻ ጥናት አቅርበዋል፡፡ የኢትዮጵያ ትምህርት ላይ ጥናቶችን አድርገዋል፡፡ ዕይታዋ ምንድን ነው? ዋና ጥናቴ እሱ ነው፡፡ ትምህርት በጣም ተዳክሟል፡፡ የተዳከመው በሁለት ምክንያት ነው ብዬ አስቀምጣለሁ፡፡ አንዱ ያለዕቅድ መስፋፋቱ ነው። የሚፈለጉ ህንፃዎች፣ አስተማሪዎች፣ መፃሕፍቶች ሳይሟሉ እንዲሁ ሠፍቷል፡፡ ሌላው ዋነኛ ምክንያት የቋንቋ ጉዳይ ነው፡፡ እንግሊዝኛ ቋንቋ አያዋጣንም፡፡ በራስ ቋንቋ መማር የህልውናና የመበት ጥያቄ ነው፡፡ ዜግነትዎ ከየትኛው ነው? ስዊድናዊ ነኝ፡፡

የአሜሪካ የስለላ ተቋም፣ አለምን ከዳር ዳር በሚያዳርስ የመረጃ መረብ፣ የውጭ ዜጎችን (የጠቅላይ ሚኒስትሮችና የፕሬዚዳንቶች ጭምር) የስልክና የኢሜይል ልውውጦችን የቱን ያህል በስፋት እንደሚሰልል ሲታይ ጉድ ያሰኛል። በእርግጥ የስለላ ተቋሙ የአሜሪካ ዜጐችን በዘፈቀደ አልሰልልም ብሏል፡፡ የዜጐች የግል ሕይወትና የመልእክት ልውውጥ በመንግስት መነካት እንደሌለበት በአገሪቱ ሕገመንግስት ታውጇላ። የዜጐችን የስልክ እና የኢሜይል መልእክት የምበረብረው፣ በተጠርጣሪዎች ላይ በማተኮርና ፍርድ ቤትን በማስፈቀድ ብቻ ነው ይላል - የአሜሪካ የስለላ ተቋም። ታዲያ “ፍርድ ቤት” ሲባል፣ የወትሮው አይነት አይደለም። በሚስጥር የሚሰራ ልዩ ፍርድ ቤት ነው። ማዘዣ ወረቀቱም በሚስጥር የሚጠበቅ ስለሆነ፣ ከጊዜ በኋላ የፍርድ ቤቱን ውሳኔዎችና ትዕዛዞች መመርመር ያስቸግራል። ፍርድ ቤትን ማስፈቀድ በኢትዮጵያ አይሰራም በእውነቱ፣ እንዲህ አይነቱ ድብቅ የፍርድ ቤት አሰራር፣ ከታላቋ የነፃነት አገር (ከአሜሪካ) የሚጠበቅ አይደለም።

ለማንኛውም፣ የስለላ ተቋሙ “የፍርድ ቤት” ማዘዣ በማቅረብ ባለፉት አምስት አመታት የተለያዩ መረጃዎችን ሲወስድ ቆይቷል፡፡ ጉግል፣ ያሁ፣ ሆትሜይል፣ ፌስቡክ እንዲሁም ኤቲኤንድ ቲ የመሳሰሉ የኢንተርኔት እና የስልክ ኩባንያዎችም፣ የመቶ ሺ ገደማ ደንበኞች መረጃ ለስለላ ተቋሙ ለማስረከብ መገደዳቸውን ገልፀዋል። ኩባንያዎቹ የሕግ ግዴታ ሆኖባቸው እንጂ፣ የአንድም ሰው መረጃ አሳልፈው መስጠት አይፈልጉም - እንጀራቸው ነዋ። በደንታ ቢስነት የደንበኞችን መረጃ እያወጣ ለመንግስት የሚዘረግፍ ኩባንያ፣ የቱንም ያህል ግዙፍ ቢሆን መንኮታኮቱና በአጭር መቀጨቱ አይቀርም። ደንበኞቹ ይሸሹታል፤ ፊታቸውን ወደ ሌላ አገልግሎት ሰጪ ኩባንያ በማዞር ጀርባቸውን ሲሰጡት፣ በኪሳራ ይፈራርሳል። ኩባንያዎቹ እንጀራቸውን ማጣት አይፈልጉም፤ እናም በተቻላቸው መጠን የደንበኞቻቸውን መረጃ ለመጠበቅ በሚያደርጉት ጥረት ለመንግስት ትልቅ ፈተና መሆናቸው አይገርምም።

በእኛ አገር ግን፣ መንግስት ይሄ ሁሉ ጣጣ አይኖርበትም። የኢንተርኔትና የስልክ አግልግሎት ሁሉ በመንግስት እጅ ነዋ። በፈለገ ጊዜ ባሰኘው መጠን፣ የስልክ ንግግሮችን ሲያዳምጥ ቢያድር፣ የፅሁፍ መልእክቶችን ሲበረብር ቢውል ማንም አያውቅም። ኢትዮ ቴሌኮም ደንበኞች ይሸሹኛል ብሎ አይሰጋም። ከቴሌ ሸሽተን የት ልንደርስ! ሌላ አማራጭ የለንም። እናም፣ ኢትዮ ቴሌኮም የደንበኞችን መረጃ አሳልፎ ላለመስጠትና ጠብቆ ለመያዝ የሚገፋፋ ጫና የለበትም። በአጭሩ፤ የስልክ እና የኢንተርኔት ግንኙነታችን በሙሉ በመንግስት እጅ ነው። የሰዎችን የስልክ እና የኢሜይል ግንኙነትን ለመጥለፍ ፖሊስ ፍ/ቤትን ማስፈቀድ እንደማያስፈልገው፣ የፀረ ሽብር ህጉ ይደነግጋል “ሁሉም በእጄ ሁሉም በደጄ” ነው ነገሩ፡፡ በፍ/ቤት ያልተፈቀደ ድብቅ ስለላስ? የአሜሪካ የስለላ ተቋም በ“ፍርድ ቤት” ማዘዣ አማካኝነት የሚሰበስባቸው መረጃዎች አያረኩትም። ተጨማሪ ብዙ መረጃ ለመሰብሰብ፣ በተለያዩ የኢንተርኔትና የስልክ ኩባንያዎች ላይ በድብቅ ስለላ እንደሚያካሂድ ባለፈው ሳምንት የተሰራጩ ዘገባዎች ገልጸዋል።

እንዴት በሉ። የአሜሪካ የስለላ ተቋም፣ ያለ “ፍርድ ቤት” ማዘዣ የጐግል ወይም የማይክሮሶፍት የመረጃ ማዕከላትን መበርበር አይችልም። በድብቅ መሰለልም ቀላል አይሆንለትም። በቴክኖሎጂ የተራቀቁት ኩባንያዎች፣ የየራሳቸው የመረጃ ማዕከላት ላይ ከፍተኛ ጥበቃ ያካሂዳሉ። የመረጃ ማዕከላትን የሚያገናኙ የስልክና የኢንተርኔት ማስተላለፊያ (የፋይበር ኦፕቲክስ) መስመሮችስ? አገር አቋራጭ መስመሮች ላይ፣ ከጫፍ እስከ ጫፍ ጥበቃ ማካሄድ ከባድ ነው። የስለላ ተቋሙም፣ የኢንተርኔት ኩባንያዎች ዋና ዋና የግንኙነት መስመሮችን በድብቅ በመጥለፍ ነው መረጃዎችን እንደሚሰበስብ የተዘገበው። በእርግጥ፣ በዘገባዎቹ ምክንያት ከፍተኛ ጫና እንደሚደርስበት የተገነዘበው የስለላ ተቋሙ፣ ሳይውል ሳያድር ዘገባዎቹን አስተባብሏል - “የኩባንያዎቹ የመረጃ ማዕከላት ላይ ስለላ አላካሄድኩም” በማለት። “የግንኙነት መስመሮች ላይስ ስለላ አካሂደሃል ወይ?” ተብሎ ሲጠየቅም የተቋሙ ምላሽ ተመሳሳይ ነው። “የመረጃ ማዕከላት ላይ ስለላ አላካሄድኩም” የሚል ሆኗል የተቋሙ ምላሽ፡፡ አጣብቂኝ ውስጥ የገባ ይመስላል፡፡

በአገራችን ግን፣ መንግስት በድብቅ መሰለል አያስፈልገውም፤ ውዝግብና ጭቅጭቅ ውስጥ የሚገባበት ምክንያትም የለም። የስልክ እና የኢንተርኔት ግንኝነቶቻችንን የሚያከማቹ የመረጃ ማዕከሎች በሙሉ በመንግስት እጅ ናቸው። የስልክ ንግግሮችን ጨምሮ በኤሌክትሮኒክስ ዘዴ የምናካሂዳቸው ግንኝነቶችን የሚያመላልሱ ዋና ዋና የመረጃ ማስተላለፊያ (የፋይበር ኦፕቲክስ) መስመሮችም የመንግስት ናቸው። ያሻውን ቢያደርግ ማን ይጠይቀዋል? “1ለ5” ማደራጀት ያልቻሉ፣ ለስለላ ይደክማሉ መቼም፣ የአሜሪካ የስለላ ተቋም፣ የስልክና የኢሜይል ልውውጦችን እየጠለፈ የሚሰበስበው፣ ማን መቼ ከማን ጋር እንደተገናኘና ምን እንዳወራ ለመሰለል ነው። የኛ አገር መንግስት ግን፣ መረጃ ለመሰብሰብ መባተል አያስፈልገውም። ማን መቼ ከማን ጋር እንደሚገናኝ ለማወቅ አይደክምም። ይልቁንስ፣ በ“1ለ5” አደረጃጀት ማን ከማን ጋር መገናኘት እንዳለበት ትዕዛዝ ያስተላልፋል። በትምህርት ቤትም ሆነ በስራ ቦታ፣ በገጠርም ሆነ በከተማ፣ “1ለ5” እንዲደራጁ የታዘዙ ዜጎች፣ በሳምንት ሁለት ቀን በየትኛው ሰዓት መገናኘት እንዳለባቸው መመሪያ የሚመጣባቸው ከመንግስት አካላት ነው። ተገናኝተው ምን ምን ማውራት እንዳለባቸውም ጭምር ትዕዛዝ ይደርሳቸዋል።

ታዲያ፣ የዜጎችን ህይወት በእጁ አስገብቶ ኑሯቸውን በትዕዛዝ የሚመራ መንግስት፣ ለምን ብሎ ይሰልላቸዋል? የአሜሪካ መንግስት የሰዎችን የመኪናና የአፓርትመንት ኪራይ በድብቅ ለመሰለል ይጣጣራል፡፡ ሰዎች የት እንዳደሩ ወዴት እንደተጓዙ ለማወቅም በስውር ይጣጣራል፡፡ የአገራችን መንግስት ግን ለድብብቆሽ ጊዜ አያጠፋም፡፡ እያንዳንዱ የቤት እና የመኪና አከራይ፣ የየእለቱን መረጃ መዝግቦ፣ በራሱ ወጪ መጥቶ ያስረከበኝ በማለት በኢቲቪ መመሪያ ያስተላልፋል፡፡ አዋጅ ማርቀቅና ማጽደቅ፣ ወይም ደንብ ማዘጋጀት እንኳ አያስፈልገውም፡፡ የዜጐች የመንቀሳቀስ ነፃነት በህገመንግስት በግልጽ እውቅና ቢሰጠውም፤ ሰዎች ከከተማ ከተማ በማታ እንዳይንቀሱ በመግለጫ ተከልክለው የለ! በትራንስፖርት ሚኒስቴር ተግባራዊ የተደረገ “የሰዓት እላፊ” ልንለው እንችላለን፡፡ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በበኩሉ፤ ወደ አረብ አገራት መሄድ ተከልክሏል የሚል መግለጫ አውጥቷል፡፡ ህጋዊውን ስርዓት ተከትለው ምዝገባ በማካሄድ በየአመቱ በአማካይ 130ሺ ኢትዮጵያውያን ለስራ ወደ አረብ አገራት ሲሄዱ ቆይተዋል፡፡

በዚህ መሃል ነው፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ድንገት ተነስቶ፣ “ጉዳት እንዳይደርስባችሁ ስለምጨነቅላችሁ እንዳትጓዙ አዝዣለሁ” የሚል መግለጫ ያወጣው፡፡ የመንቀሳቀስ ነፃነት የሚባለው የህገመንግስት አንቀጽ የት ደረሰ? የገንዘብ ሚኒስቴርስ፣ “ደሞዛችሁን እንዳታባክኑ ስለምጨነቅላችሁ፣ ግማሽ ደሞዛችሁን እንድትቆጥቡ አዝዣለሁ” ብሎ መግለጫ ማውጣት አይችልም? “በራሴ ደሞዝና ገቢ መንግስት ምን አገባው” ብላችሁ ታስቡ ይሆናል፡፡ በእርግጥም የንብረት ባለቤትነትና ነፃነት የሚሉ የህገመንግስት አንቀፆች አሉ፡፡ ግን በርካታ አነስተኛና ጥቃቅን ተቋማት፣ ለቁጠባ ገንዘብ ለማስቀመጥ እንደሚገደዱ አታውቁም? የግል ባንኮችም፣ በየአመቱ ከሚሰጡት የብድር መጠን ከሩብ በላይ የሚሆነውን የመንግስት ቦንድ በመግዛት እንዲቆጥቡ ግዴታ ከተጣለባቸው ሁለት አመት አልፏቸዋል፡፡ በአጭሩ፣ መንግስት የዜጐችን እንቅስቃሴና የገንዘብ ልውውጥን ለመሰለል የሚደክምበት ምክንያት የለም፡፡

በየትኛው ሰዓት እና ወዴት አገር መጓዝ እንደምችል፣ ከደሞዛችን ምን ያህል መቆጠብና ለአስቤዛ እንደሚፈቀድልን ወይም እንደማይፈቀድልን በመግለጫ ማዘዝ እየቻለ፣ መንግስት የስለላ ጣጣ ውስጥ መግባት አይኖርበትም፡፡ የትምህርት ቤት ምዝገባና የስራ ስምሪትን፣ የሸቀጦች ግዢና ሽያጭን በተመለከተ መረጃ ለመሰብሰብ እነ አሜሪካ መከራቸውን ሊያዩ ይችላሉ፡፡ የአገራችን መንግስት ግን፣ ተማሪዎች የትኛው ዩኒቨርሲቲ ውስጥ መማር፣ በየትኛው የአሽከርካሪዎች ማሰልጠኛ መለማመድ እንደሚችሉ ምደባ ማካሄድና መወሰን ይችላል፡፡ የሸቀጦችን ግዢ እና ሽያጭን ከነዋጋ ተመናቸው በመግለጫ ትዕዛዝ እንደሚያስተላልፍም እናውቃለን፡፡ ስኳርና ዘይት በጅምላ የሚከፋፈለው ለሸማቾች ማህበር ብቻ ነው ተባለ፡፡ ደግሞም በስኳርና በዘይት ብቻ አይደለም የዋጋ ተመን የወጣብን፡፡ የበግ እና የፍየል ቆዳ ከ40 ብር በላይ ማንም መሸጥ የለበትም የሚል መግለጫም ሰምተናል፡፡

አሁን ደግሞ የእንስሳትና የቆዳ ገበያ ውስጥ እነማን ሻጭ እና ገዢ ለመሆን እንደሚፈቀድላቸው የሚደነግግ ህግ ተዘጋጅቷል፡፡ ታዲያ መንግስት ለምን ሲባል፣ የስለላ ጣጣ ውስጥ ይገባል፤ ሁሉም በእጁ ሁሉም በደጁ፡፡ ዜጎች የሕይወታቸው ብቸኛ ባለቤት ሆነው እንደየፍላጎታቸው ካሰኛቸው ሰው ጋር መገናኘትና መደራጀት፣ መስራትና መገበያየት ሲችሉ፣ ኑሯቸውን በየራሳቸው የግል ፈቃድ በነፃነት እየመሩ፣ እንደየሃሳባቸው ያመኑበትን ነገር መናገርና መፃፍ ሲችሉ… ያኔ፣ “ማን ከማን ጋር እየተገናኘ ይሆን? ማን ምን እያወራ ይሆን?” ብሎ መሰለል ወግ ነው። ዜጎችን መሰለል፣ ተገቢና ጥሩ ስራ ባይሆንም፣ “ትርጉም” ይኖረዋል። የእያንዳንዱን ሰው ገመና ለማወቅ የሚደረግ ስለላ ነዋ። የዜጎች ግንኙነት ከመንግስት በሚመጣ የ“1ለ5” አደረጃጀት የሚታዘዝ፣ የዜጎች ወሬ ከመንግስት በሚመጣ “አጀንዳ” የሚመራ፣ የዜጐች ስራ እና ግብይት በመንግስት የስምሪትና የተመን መግለጫ የሚቦካ የሚከካ ሲሆን ግን፣ ስለላ የሚባል ነገር ጨርሶ “ትርጉም” ያጣል። የዜጎች ሕይወትና ኑሮ በመንግስት እጅ ከሆነ፣ ለስለላ የሚያነሳሳ “ገመና” ከየት ይመጣል?

የአሜሪካ የስለላ ተቋም፣ አለምን ከዳር ዳር በሚያዳርስ የመረጃ መረብ፣ የውጭ ዜጎችን (የጠቅላይ ሚኒስትሮችና የፕሬዚዳንቶች ጭምር) የስልክና የኢሜይል ልውውጦችን የቱን ያህል በስፋት እንደሚሰልል ሲታይ ጉድ ያሰኛል። በእርግጥ የስለላ ተቋሙ የአሜሪካ ዜጐችን በዘፈቀደ አልሰልልም ብሏል፡፡ የዜጐች የግል ሕይወትና የመልእክት ልውውጥ በመንግስት መነካት እንደሌለበት በአገሪቱ ሕገመንግስት ታውጇላ። የዜጐችን የስልክ እና የኢሜይል መልእክት የምበረብረው፣ በተጠርጣሪዎች ላይ በማተኮርና ፍርድ ቤትን በማስፈቀድ ብቻ ነው ይላል - የአሜሪካ የስለላ ተቋም። ታዲያ “ፍርድ ቤት” ሲባል፣ የወትሮው አይነት አይደለም። በሚስጥር የሚሰራ ልዩ ፍርድ ቤት ነው። ማዘዣ ወረቀቱም በሚስጥር የሚጠበቅ ስለሆነ፣ ከጊዜ በኋላ የፍርድ ቤቱን ውሳኔዎችና ትዕዛዞች መመርመር ያስቸግራል። ፍርድ ቤትን ማስፈቀድ በኢትዮጵያ አይሰራም በእውነቱ፣ እንዲህ አይነቱ ድብቅ የፍርድ ቤት አሰራር፣ ከታላቋ የነፃነት አገር (ከአሜሪካ) የሚጠበቅ አይደለም።

ለማንኛውም፣ የስለላ ተቋሙ “የፍርድ ቤት” ማዘዣ በማቅረብ ባለፉት አምስት አመታት የተለያዩ መረጃዎችን ሲወስድ ቆይቷል፡፡ ጉግል፣ ያሁ፣ ሆትሜይል፣ ፌስቡክ እንዲሁም ኤቲኤንድ ቲ የመሳሰሉ የኢንተርኔት እና የስልክ ኩባንያዎችም፣ የመቶ ሺ ገደማ ደንበኞች መረጃ ለስለላ ተቋሙ ለማስረከብ መገደዳቸውን ገልፀዋል። ኩባንያዎቹ የሕግ ግዴታ ሆኖባቸው እንጂ፣ የአንድም ሰው መረጃ አሳልፈው መስጠት አይፈልጉም - እንጀራቸው ነዋ። በደንታ ቢስነት የደንበኞችን መረጃ እያወጣ ለመንግስት የሚዘረግፍ ኩባንያ፣ የቱንም ያህል ግዙፍ ቢሆን መንኮታኮቱና በአጭር መቀጨቱ አይቀርም። ደንበኞቹ ይሸሹታል፤ ፊታቸውን ወደ ሌላ አገልግሎት ሰጪ ኩባንያ በማዞር ጀርባቸውን ሲሰጡት፣ በኪሳራ ይፈራርሳል። ኩባንያዎቹ እንጀራቸውን ማጣት አይፈልጉም፤ እናም በተቻላቸው መጠን የደንበኞቻቸውን መረጃ ለመጠበቅ በሚያደርጉት ጥረት ለመንግስት ትልቅ ፈተና መሆናቸው አይገርምም።

በእኛ አገር ግን፣ መንግስት ይሄ ሁሉ ጣጣ አይኖርበትም። የኢንተርኔትና የስልክ አግልግሎት ሁሉ በመንግስት እጅ ነዋ። በፈለገ ጊዜ ባሰኘው መጠን፣ የስልክ ንግግሮችን ሲያዳምጥ ቢያድር፣ የፅሁፍ መልእክቶችን ሲበረብር ቢውል ማንም አያውቅም። ኢትዮ ቴሌኮም ደንበኞች ይሸሹኛል ብሎ አይሰጋም። ከቴሌ ሸሽተን የት ልንደርስ! ሌላ አማራጭ የለንም። እናም፣ ኢትዮ ቴሌኮም የደንበኞችን መረጃ አሳልፎ ላለመስጠትና ጠብቆ ለመያዝ የሚገፋፋ ጫና የለበትም። በአጭሩ፤ የስልክ እና የኢንተርኔት ግንኙነታችን በሙሉ በመንግስት እጅ ነው። የሰዎችን የስልክ እና የኢሜይል ግንኙነትን ለመጥለፍ ፖሊስ ፍ/ቤትን ማስፈቀድ እንደማያስፈልገው፣ የፀረ ሽብር ህጉ ይደነግጋል “ሁሉም በእጄ ሁሉም በደጄ” ነው ነገሩ፡፡ በፍ/ቤት ያልተፈቀደ ድብቅ ስለላስ? የአሜሪካ የስለላ ተቋም በ“ፍርድ ቤት” ማዘዣ አማካኝነት የሚሰበስባቸው መረጃዎች አያረኩትም። ተጨማሪ ብዙ መረጃ ለመሰብሰብ፣ በተለያዩ የኢንተርኔትና የስልክ ኩባንያዎች ላይ በድብቅ ስለላ እንደሚያካሂድ ባለፈው ሳምንት የተሰራጩ ዘገባዎች ገልጸዋል።

እንዴት በሉ። የአሜሪካ የስለላ ተቋም፣ ያለ “ፍርድ ቤት” ማዘዣ የጐግል ወይም የማይክሮሶፍት የመረጃ ማዕከላትን መበርበር አይችልም። በድብቅ መሰለልም ቀላል አይሆንለትም። በቴክኖሎጂ የተራቀቁት ኩባንያዎች፣ የየራሳቸው የመረጃ ማዕከላት ላይ ከፍተኛ ጥበቃ ያካሂዳሉ። የመረጃ ማዕከላትን የሚያገናኙ የስልክና የኢንተርኔት ማስተላለፊያ (የፋይበር ኦፕቲክስ) መስመሮችስ? አገር አቋራጭ መስመሮች ላይ፣ ከጫፍ እስከ ጫፍ ጥበቃ ማካሄድ ከባድ ነው። የስለላ ተቋሙም፣ የኢንተርኔት ኩባንያዎች ዋና ዋና የግንኙነት መስመሮችን በድብቅ በመጥለፍ ነው መረጃዎችን እንደሚሰበስብ የተዘገበው። በእርግጥ፣ በዘገባዎቹ ምክንያት ከፍተኛ ጫና እንደሚደርስበት የተገነዘበው የስለላ ተቋሙ፣ ሳይውል ሳያድር ዘገባዎቹን አስተባብሏል - “የኩባንያዎቹ የመረጃ ማዕከላት ላይ ስለላ አላካሄድኩም” በማለት። “የግንኙነት መስመሮች ላይስ ስለላ አካሂደሃል ወይ?” ተብሎ ሲጠየቅም የተቋሙ ምላሽ ተመሳሳይ ነው። “የመረጃ ማዕከላት ላይ ስለላ አላካሄድኩም” የሚል ሆኗል የተቋሙ ምላሽ፡፡ አጣብቂኝ ውስጥ የገባ ይመስላል፡፡

በአገራችን ግን፣ መንግስት በድብቅ መሰለል አያስፈልገውም፤ ውዝግብና ጭቅጭቅ ውስጥ የሚገባበት ምክንያትም የለም። የስልክ እና የኢንተርኔት ግንኝነቶቻችንን የሚያከማቹ የመረጃ ማዕከሎች በሙሉ በመንግስት እጅ ናቸው። የስልክ ንግግሮችን ጨምሮ በኤሌክትሮኒክስ ዘዴ የምናካሂዳቸው ግንኝነቶችን የሚያመላልሱ ዋና ዋና የመረጃ ማስተላለፊያ (የፋይበር ኦፕቲክስ) መስመሮችም የመንግስት ናቸው። ያሻውን ቢያደርግ ማን ይጠይቀዋል? “1ለ5” ማደራጀት ያልቻሉ፣ ለስለላ ይደክማሉ መቼም፣ የአሜሪካ የስለላ ተቋም፣ የስልክና የኢሜይል ልውውጦችን እየጠለፈ የሚሰበስበው፣ ማን መቼ ከማን ጋር እንደተገናኘና ምን እንዳወራ ለመሰለል ነው። የኛ አገር መንግስት ግን፣ መረጃ ለመሰብሰብ መባተል አያስፈልገውም። ማን መቼ ከማን ጋር እንደሚገናኝ ለማወቅ አይደክምም። ይልቁንስ፣ በ“1ለ5” አደረጃጀት ማን ከማን ጋር መገናኘት እንዳለበት ትዕዛዝ ያስተላልፋል። በትምህርት ቤትም ሆነ በስራ ቦታ፣ በገጠርም ሆነ በከተማ፣ “1ለ5” እንዲደራጁ የታዘዙ ዜጎች፣ በሳምንት ሁለት ቀን በየትኛው ሰዓት መገናኘት እንዳለባቸው መመሪያ የሚመጣባቸው ከመንግስት አካላት ነው። ተገናኝተው ምን ምን ማውራት እንዳለባቸውም ጭምር ትዕዛዝ ይደርሳቸዋል።

ታዲያ፣ የዜጎችን ህይወት በእጁ አስገብቶ ኑሯቸውን በትዕዛዝ የሚመራ መንግስት፣ ለምን ብሎ ይሰልላቸዋል? የአሜሪካ መንግስት የሰዎችን የመኪናና የአፓርትመንት ኪራይ በድብቅ ለመሰለል ይጣጣራል፡፡ ሰዎች የት እንዳደሩ ወዴት እንደተጓዙ ለማወቅም በስውር ይጣጣራል፡፡ የአገራችን መንግስት ግን ለድብብቆሽ ጊዜ አያጠፋም፡፡ እያንዳንዱ የቤት እና የመኪና አከራይ፣ የየእለቱን መረጃ መዝግቦ፣ በራሱ ወጪ መጥቶ ያስረከበኝ በማለት በኢቲቪ መመሪያ ያስተላልፋል፡፡ አዋጅ ማርቀቅና ማጽደቅ፣ ወይም ደንብ ማዘጋጀት እንኳ አያስፈልገውም፡፡ የዜጐች የመንቀሳቀስ ነፃነት በህገመንግስት በግልጽ እውቅና ቢሰጠውም፤ ሰዎች ከከተማ ከተማ በማታ እንዳይንቀሱ በመግለጫ ተከልክለው የለ! በትራንስፖርት ሚኒስቴር ተግባራዊ የተደረገ “የሰዓት እላፊ” ልንለው እንችላለን፡፡ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በበኩሉ፤ ወደ አረብ አገራት መሄድ ተከልክሏል የሚል መግለጫ አውጥቷል፡፡ ህጋዊውን ስርዓት ተከትለው ምዝገባ በማካሄድ በየአመቱ በአማካይ 130ሺ ኢትዮጵያውያን ለስራ ወደ አረብ አገራት ሲሄዱ ቆይተዋል፡፡

በዚህ መሃል ነው፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ድንገት ተነስቶ፣ “ጉዳት እንዳይደርስባችሁ ስለምጨነቅላችሁ እንዳትጓዙ አዝዣለሁ” የሚል መግለጫ ያወጣው፡፡ የመንቀሳቀስ ነፃነት የሚባለው የህገመንግስት አንቀጽ የት ደረሰ? የገንዘብ ሚኒስቴርስ፣ “ደሞዛችሁን እንዳታባክኑ ስለምጨነቅላችሁ፣ ግማሽ ደሞዛችሁን እንድትቆጥቡ አዝዣለሁ” ብሎ መግለጫ ማውጣት አይችልም? “በራሴ ደሞዝና ገቢ መንግስት ምን አገባው” ብላችሁ ታስቡ ይሆናል፡፡ በእርግጥም የንብረት ባለቤትነትና ነፃነት የሚሉ የህገመንግስት አንቀፆች አሉ፡፡ ግን በርካታ አነስተኛና ጥቃቅን ተቋማት፣ ለቁጠባ ገንዘብ ለማስቀመጥ እንደሚገደዱ አታውቁም? የግል ባንኮችም፣ በየአመቱ ከሚሰጡት የብድር መጠን ከሩብ በላይ የሚሆነውን የመንግስት ቦንድ በመግዛት እንዲቆጥቡ ግዴታ ከተጣለባቸው ሁለት አመት አልፏቸዋል፡፡ በአጭሩ፣ መንግስት የዜጐችን እንቅስቃሴና የገንዘብ ልውውጥን ለመሰለል የሚደክምበት ምክንያት የለም፡፡

በየትኛው ሰዓት እና ወዴት አገር መጓዝ እንደምችል፣ ከደሞዛችን ምን ያህል መቆጠብና ለአስቤዛ እንደሚፈቀድልን ወይም እንደማይፈቀድልን በመግለጫ ማዘዝ እየቻለ፣ መንግስት የስለላ ጣጣ ውስጥ መግባት አይኖርበትም፡፡ የትምህርት ቤት ምዝገባና የስራ ስምሪትን፣ የሸቀጦች ግዢና ሽያጭን በተመለከተ መረጃ ለመሰብሰብ እነ አሜሪካ መከራቸውን ሊያዩ ይችላሉ፡፡ የአገራችን መንግስት ግን፣ ተማሪዎች የትኛው ዩኒቨርሲቲ ውስጥ መማር፣ በየትኛው የአሽከርካሪዎች ማሰልጠኛ መለማመድ እንደሚችሉ ምደባ ማካሄድና መወሰን ይችላል፡፡ የሸቀጦችን ግዢ እና ሽያጭን ከነዋጋ ተመናቸው በመግለጫ ትዕዛዝ እንደሚያስተላልፍም እናውቃለን፡፡ ስኳርና ዘይት በጅምላ የሚከፋፈለው ለሸማቾች ማህበር ብቻ ነው ተባለ፡፡ ደግሞም በስኳርና በዘይት ብቻ አይደለም የዋጋ ተመን የወጣብን፡፡ የበግ እና የፍየል ቆዳ ከ40 ብር በላይ ማንም መሸጥ የለበትም የሚል መግለጫም ሰምተናል፡፡

አሁን ደግሞ የእንስሳትና የቆዳ ገበያ ውስጥ እነማን ሻጭ እና ገዢ ለመሆን እንደሚፈቀድላቸው የሚደነግግ ህግ ተዘጋጅቷል፡፡ ታዲያ መንግስት ለምን ሲባል፣ የስለላ ጣጣ ውስጥ ይገባል፤ ሁሉም በእጁ ሁሉም በደጁ፡፡ ዜጎች የሕይወታቸው ብቸኛ ባለቤት ሆነው እንደየፍላጎታቸው ካሰኛቸው ሰው ጋር መገናኘትና መደራጀት፣ መስራትና መገበያየት ሲችሉ፣ ኑሯቸውን በየራሳቸው የግል ፈቃድ በነፃነት እየመሩ፣ እንደየሃሳባቸው ያመኑበትን ነገር መናገርና መፃፍ ሲችሉ… ያኔ፣ “ማን ከማን ጋር እየተገናኘ ይሆን? ማን ምን እያወራ ይሆን?” ብሎ መሰለል ወግ ነው። ዜጎችን መሰለል፣ ተገቢና ጥሩ ስራ ባይሆንም፣ “ትርጉም” ይኖረዋል። የእያንዳንዱን ሰው ገመና ለማወቅ የሚደረግ ስለላ ነዋ። የዜጎች ግንኙነት ከመንግስት በሚመጣ የ“1ለ5” አደረጃጀት የሚታዘዝ፣ የዜጎች ወሬ ከመንግስት በሚመጣ “አጀንዳ” የሚመራ፣ የዜጐች ስራ እና ግብይት በመንግስት የስምሪትና የተመን መግለጫ የሚቦካ የሚከካ ሲሆን ግን፣ ስለላ የሚባል ነገር ጨርሶ “ትርጉም” ያጣል። የዜጎች ሕይወትና ኑሮ በመንግስት እጅ ከሆነ፣ ለስለላ የሚያነሳሳ “ገመና” ከየት ይመጣል?

            ኒውዮርክ ታይምስ ባለፈው መስከረም መግቢያ ላይ እንደዘገበው፣ የአሜሪካ ብሄራዊ የፀጥታ ኤጀንሲ (NSA) በየቀኑ 4 ቢሊዮን የስልክ እና የኢሜይል መረጃዎችን እየመዘገበ ያከማቻል። ዎልስትሪት ጆርናል በበኩሉ፣ NSA በአሜሪካ በየእለቱ በቢሊዮን ከሚቆጠሩ የኢሜይል ልውውጦች መካከል 75 በመቶ ያህሉን የመከታተል አቅም እንዳለው ገልጿል። ስለላው የስልክ እና የኢሜይል ብቻ ሳይሆን፣ የጉዞና የሆቴል አዳርን፣ የመኪናና የአፓርትመንት ኪራይን ጨምሮ የማያካልለው የህይወት ገጽታ የለም፡፡ የሱፐርማርኬት ሸቀጦች ግዥና ሽያጭን፣ የባንክ ብድርና የገንዘብ ልውውጥን፣ የትምህርት ቤት ምዝገባና የስራ ቅጥርን የሚገልፁ መረጃዎች ሁሉ ስለላ ይካሄድባቸዋል፡፡ የሚያመልጥ ነገር የለም የሞባይል እና የኢንተርኔት ስለላ በእርግጥ፣ “የስልክና የኢንተርኔት ግንኙነቶችን እየተከታተለ መረጃዎችን ይሰበስባል” ማለት፣ “ጆሮውን ደቅኖ ይሰማል፤ አይኑን ተክሎ ይቃኛል፤ በየሴኮንዱም ድምፅና ፅሁፍ፣ ፎቶና ቪዲዮ እየቀረፀ ያከማቻል” ማለት ላይሆን ይችላል።

ስልክ ደውለን ስናነጋግር፣ ሞባይላችን መረጃዎችን ይመዘግብ የለ? የንግግራችንን ድምፅ ባንቀርፀውም እንኳ፣ ወደ የትኛው የስልክ ቁጥር መቼ እንደደወልን ወይም እንደተደወለልን፣ ለምን ያህል ደቂቃ እንዳነጋገርን ማወቅ እንችላለን። እንዲህ አይነቱ መረጃ “ሜታዳታ” ይሉታል። የተቀረፀ ንግግር ደግሞ “ዳታ” ብለው ይጠሩታል። ኮምፒዩተር ላይ ፋይሎችን ስንከፍት የምናገኘውን ድምፅ ወይም ቪዲዮ፣ ፎቶ ወይም ፅሁፍ፣ “ዳታ” ይሉታል። የፋይሎች ስምና አይነታቸውን፣ መጠንና ቦታቸውን፣ መቼ እንደተቀመጡና መቼ እንደተከፈቱ የሚገልፅ የመረጃ ዝርዝር ደግሞ ሜታዳታ ይባላል። የአሜሪካ ብሄራዊ የፀጥታ ኤጀንሲ፣ ዜጎች በስልክ የሚያወሩትን በድምፅ እየቀረፀ፣ በኢሜይል የሚለዋወጡትን ፅሁፍ እየገለበጠ እንደማያከማች ይገልፃል።

“ማን ለማን መቼ ደወለ?፣ ለምን ያህል ደቂቃ አነጋገረ? ማን ለማን መቼ ኢሜይል ላከ?” እንዲህ የመሳሰሉ “ሜታዳታዎችን” ነው የምሰልለው ይላል NSA። ይቅርታ፣ “ሜታዳታዎችንም አከማቻለሁ እንጂ አልሰልልም” ባይ ነው NSA። “መረጃዎችን አከማቻለሁ፤ መረጃዎች ላይ አንዳች ምርመራ ወይም ስለላ የማካሂደው፣ አጠራጣሪ ፍንጭ ሲኖር ብቻ ነው” ይላል - ኤንኤስኤ። ፖፕላር ሳይንስ መጽሔት ሰሞኑን ባወጣው ዘገባው፣ የNSA አሰራር ተራራ በሚያክል የሳር ክምር ውስጥ፣ መርፌ ፈልጎ እንደማግኘት መሆኑን ያስረዳል። በአንድ ሰው ተነስቶ ሺዎችን የሚያዳርስ የስለላ ድር NSA በየእለቱ በቢሊዮን የሚቆጠሩ መረጃዎችን የሚያከማች ቢሆንም፣ ከመረጃው ብዛት የተነሳ እያንዳንዱን እየመዘዘ መመርመር አይችልም። ነገር ግን አቋራጭ ዘዴዎች አሉ። ፍንጮችን በማነፍነፍ ላይ የተመሰረተ ምርመራና ስለላ! የተቋሙ ስለላ እንዴት እንደሚካሄድ ፒኤም መፅሄት ሲያስረዳ፣ አንድ በሽብር ተግባር የሚጠረጠር ተፈላጊ የመን ውስጥ ይኖራል በማለት ይጀምራል።

ተጠርጣሪው ሞኝ ካልሆነ በቀር፣ በቀጥታ አሜሪካ ውስጥ ወደሚገኝ ምልምል አባል ስልክ አይደውልም፣ ኢሜይል አይልክም። ነገር ግን፣ እዚያው የመን ውስጥ፣ የስልክ ወይም የኢሜይል ግንኙነት ማድረጉ አይቀርም። እዚህ ላይ ነው ስለላው የሚጀምረው፡፡ ተጠርጣሪው ለማንና መቼ ደወለ? ለምን ያህል ደቂቃ አነጋገረ? ለእነማን መቼ ኢሜይል ላከ? ከእነማን መቼ ተደወለለት? …. በእነዚህ ሜታዳታዎች አማካኝነት፣ የተጠርጣሪው የግንኙነት መረብ በኮምፒዩተር ይቀናበራል። በዚህ መረብ ውስጥ መቶ ሰዎች ሊኖሩ ይችላሉ። ብዙዎቹ ከተጠርጣሪው የሽብር ተግባር ጋር ግንኙነት የሌላቸው የቤተሰብና የዘመድ ሰዎች ሊሆኑ ይችላሉ፤ በሰፈርና በቢዝነስ የሚተዋወቁም ይኖራሉ። ነገር ግን ከመካከላቸው ውስጥ አንዱ የተጠርጣሪው የሽብር ሴራ ተባባሪ፣ አለቃው ወይም ተላላኪው ሊሆን ይችላል። ግን የትኛው እንደሆነ ለይቶ ለማወቅ ያስቸግራል። እናም በደፈናው፣ መቶዎቹ ሰዎች በስልክና በኢሜል የሚያደርጉት ግንኙነት እየተመዘገበ በኮምፒዩተር ይቀናበራል - በሺ የሚቆጠሩ ሰዎችን የሚያካልል ሌላ ሰፊ መረብ ተፈጠረ ማለት ነው። እነዚህ በሺ የሚቆጠሩ ሰዎችስ ከማን ጋር ይደዋወላሉ? ሌላ የተንቦረቀቀ ሦስተኛ መረብ መሆኑ ነው፡፡

በሌላ አነጋገር፣ “የተጠርጣሪው የጓደኛ፣ ጓደኛ፣ ጓደኛ…” እየተባለ የስለላ መረብ ይዘረጋባቸዋል፡፡ እንዲህ በአንድ የመናዊ ተጠርጣሪ ዙሪያ ያጠነጠኑ በርካታ የግንኙነት መረቦች እየተለዩ ክትትል ይደረግባቸዋል። በግንኙነት መረብ ውስጥ ከተካተቱት በአስር ሺ የሚቆጠሩ የስልክ ቁጥሮች መካከል አንዱ ወይም ሁለቱ፣ በሆነ አጋጣሚ ለአንድ የአሜሪካ ነዋሪ ሲደውሉ ነው፣ በNSA ኮምፒዩተሮች ውስጥ “ቀይ መብራት” ብልጭ የሚለው። ግን ምን ዋጋ አለው? ከመካከለኛው ምስራቅ በየጊዜው የሚደወልላቸው የአሜሪካ ነዋሪዎች በብዙ ሺ የሚቆጠሩ ናቸው። ሁሉንም በተጠርጣሪነት መመርመር አይቻልም። ምን ተሻለ? NSA በየእለቱ መረጃ የሚሰበስበው የስልክና የኢሜይል ግንኙነት ላይ ብቻ አይደለም። የገንዘብ ልውውጦችንም ይመዘግባል፤ “ማን ለማን መቼ ምን ያህል ገንዘብ፣ ጌጣጌጥና ስጦታ አበረከተ?” በየደቂቃውና በየሴኮንዱ መረጃዎች እየተሰበሰቡ ይከማቻሉ። ይህም ብቻ አይደለም። “ማን፣ መቼ፣ ምን፣ ከየት ገዛ?” … በክሬዲትካርድ ከየሱፐርማርኬቱና ከየመደብሩ የተፈፀሙ የግዢ መረጃዎች ይከማቻሉ። የሆቴል እና የአፓርትመንት ክፍያዎችን፣ የትምህርት እና የስልጠና ምዝገባዎችን፣ የአውሮፕላንና የባቡር ትኬቶችን፣ የመኪና ግዢና ኪራይን በተመለከተም መረጃዎች ይሰበሰባሉ።

እነዚህ ሁሉ ይጠናቀራሉ። ግዙፍ ኮምፒዩተሮችና ተዓምረኛ ሶፍትዌሮች በአንድ የመናዊ የሽብር ተጠርጣሪ ዙሪያ የስልክና የኢሜይል ግንኘነቶቹን በመቃኘት የተጀመረው ‘ፍንጭ ፍለጋ’፣ ብቻውን ያን ያህል ጥቅም አይኖረውም፡፡ ከሌሎች መረጃዎች ጋር ሲቀናበር ግን ውጤቱ ለማመን የሚያስቸግር ይሆናል። “አንድ የአሜሪካ ነዋሪ፣ ከመካከለኛው ምስራቅ ስልክ ይደወልለታል” ከሚለው ፍንጭ በተጨማሪ፤ “መኪና መከራየትን የሚያዘወትር ነው ወይ?” ተብሎ ይፈተሻል። ከውጭ አገርስ ገንዘብ ይላክለታል? ተቀጣጣይ ነገሮችን ለመስራት የሚያገለግሉ ሸቀጦችን ከሱፐር ማርኬት ገዝቶ ያውቃል? የአክራሪዎችን ፕሮፓጋንዳ በኢንተርኔት የሚከታተል ወይም የፈንጂ አሰራርን የሚያሳዩ ድረገፆችን መመልከት የሚያበዛ ከሆነም ተጨማሪ ፍንጭ ነው። የጥቃት ኢላማ ናቸው ተብለው ወደሚገመቱ ስፍራዎች በተደጋጋሚ የተጓዘ ወይም በአቅራቢያ አፓርታማ የተከራየ ከሆነም ያስጠረጥራል።

በየጊዜው የትምህርትና የስልጠና ቦታዎችን እየለዋወጠ ከተመዘገበም እንዲሁ! እነዚህ ሁሉ፣ “የአሸባሪዎች ልዩ ባህርይ ናቸው” ተብለው የሚጠቀሱ መለያዎች ናቸው። ከእነዚህ ውስጥ ብዙዎቹን ነገሮች የሚያሟላ የአሜሪካ ነዋሪ አለ ወይ? እንዲህ አይነት ሰው፣ ያለጥርጥር ለሽብር ጥቃት የተዘጋጀ ሰው ነው። ግን አለ ወይ? ይሄ ነው የ NSA ጥያቄ። NSA አሰስ ገሰሱን ሁሉ እያሰሰ የመረጃ መአት የሚያሰባስበው፣ እንዲህ አይነት ጥያቄዎችን ለመመለስ ነው። በእርግጥ፣ እንደተራራ የገዘፈ የመረጃ ክምር ላይ መቀመጥ ብቻውን በቂ አይደለም። ያን ሁሉ መረጃ በአጭር ጊዜ መፈተሽና ለጥያቄው ምላሽ መስጠት የሚችል የኮምፒዩተር አቅምና ጥበብ ያስፈልጋል። NSA፣ ከመረጃ ክምችት በተጨማሪ፣ መረጃዎችን በፍጥነት ፈትሾና አመሳክሮ፣ አንጥሮና አቀናብሮ ምላሽ ለመስጠት የሚያስችል ግዙፍ የኮምፒዩተር አቅም አለው። ከሁሉም በላይ ደግሞ፣ የተራቀቁ የኮምፒዩተር ፕሮግራሞች (ሶፍትዌሮች) ባለቤት ነው። ከተራቀቁት ሶፍትዌሮቹ መካከል በአዲስነቱና በውስብስብነቱ የሚጠቀሰው ኤክስኪስኮር (Xkeyscore) የተሰኘው ሶፍትዌር እንደሆነ ዘጋርድያን ጋዜጣ ዘግቧል። ኤክስኪስኮር፣ መረጃዎችን አስሶና ፈልፍሎ፣ ለቅሞና አንጥሮ የማውጣት አቅሙ እጅግ ሃያል ከመሆኑ የተነሳ፣ “ብዙ ያዩና የሚያውቁ የNSA ባለሙያዎች” ሳይቀሩ አስደናቂ ትንግርት እንደሆነባቸው ዘጋርድያን ገልጿል።

ልብወለድ ይመስላል። ነገር ግን፣ በእንግሊዝ የስለላ ድርጅት ስራ ላይ የዋለው ዲሰንት (DScent) የተሰኘ ሶፍትዌር ምን ያህል ስኬታማ እንደሆነ በማየት ማነፃፀር ይቻላል። የእንግሊዙ ሶፍትዌር (ዲሰንት) “ማን፣ ምን አይነት ሸቀጦችን መቼ ሸመተ? ማን፣ መቼ፣ የት የት ቦታ ሄደ?” የሚሉ ጥያቄዎች ላይ በማተኮር ምርመራ የሚያከናውን መሆኑን ፒ ኤም መፅሔት ዘግቧል። ሶፍትዌሩ የሰዎችን የሸቀጥ ግዢና የጉዞ መዳረሻ በመፈተሽ፣ አሸባሪዎችን ለይቶ ማወቅ ይችላል ብሏል መጽሔቱ። ሶፍትዌሩ ሁሉንም አሸባሪዎች ለይቶ ያውቃል ማለት ነው? አይደለም። ነገር ግን፣ አንድ የሽብር ጥቃት ለመፈፀም ዝግጅት ከሚያካሂዱ አስር አሸባሪዎች መካከል 6ቱን ለይቶ ለማወቅ እንደሚችል በሙከራ ተረጋግጧል ሲል ፒኤም መፅሄት ዘግቧል። የእንግሊዙ የስለላ ድርጅት የሚጠቀምበት ሶፍትዌር (ዲሰንት) ጉደኛ ነው ቢባል የሚበዛበት አይመስልም። የአሜሪካው ኤክስኪስኮር የተሰኘው ሴፍትዌር ደግሞ፤ ከዲሰንት በእጅጉ የላቀ እንደሆነ ተነግሮለታል። ለምሳሌ፣ “ተጠርጣሪው ሰውዬ የጀርመንኛ ቋንቋ የሚናገር የፓኪስታን ነዋሪ እንደሆነ መረጃ ደርሶናል። ሰውዬውን እንዴት ማግኘት እንችላለን?” የሚል ጥያቄ ይነሳል። ኤክስኪስኮር ለዚህ ጥያቄ ፈጣን ምላሽ መስጠት ይችላል። “አንድ የማይታወቅ ሰው የሆነ አገር ውስጥ፣ ለሽብር ጥቃት የተመረጡ ቦታዎችን በኢንተርኔት ሲቃኝ ነበር። የኢሜይል አድራሻውን ማወቅ እችላለሁ?” … ኤክስኪስኮር አሁንም ፈጣን ምላሽ ያቀርባል። ተአምረኛ ሶፍትዌር ነው። አለምን የሚሸፍን የዘመናችን የስለላ መረብ በኢንተርኔትና በስልክ የሚተላለፉ ድምፆችን፣ ፅሁፎችን፣ ፎቶዎችንንና ቪዲዮዎችን በሙሉ በደፈናው መሰለልና ቀርፆ ማከማቸት አይቻልም።

በመላው አለም የሚመነጨውና የሚሰራጨው የኤሌክትሮኒክስ መረጃ እጅግ ብዙ ነው። በየቀኑ 7.8 ቢሊዮን ጊጋባይት መረጃ ይመነጫል። በየእለቱ የሚመነጨውን ዲጂታል መረጃ ለመቅረፅና ለማከማቸት፣ ምን ያህል ባለ አራት ጊጋባይት ፍላሾች ወይም ዲቪዲዎች እንደሚያስፈልጉ አስቡት። ሁለት ቢሊዮን ፍላሽ! ወይም ሁለት ቢሊዮን የዲቪዲ ዲስኮች! በየቀኑ! 35 ሚሊዮን መፃህፍት ከያዘው ግዙፉ የኮንግረስ ቤተመፃህፍት ጋር ማነፃፀርም ይቻላል። ዲጂታል መረጃዎችን በሙሉ ማከማቸት፣ በየእለቱ ስምንት መቶ ሺ ተጨማሪ ግዙፍ ቤተመፃህፍት እንደመገንባት ነው። ይሄን ሁሉ ጥሬ መረጃ (ዳታ) በየእለቱ መከታተልና ቀርፆ ማከማቸት አይቻልም። የመፃህፍቱን ርዕስ፣ ደራሲ፣ አሳታሚ፣ ወዘተ መዝግቦ ማስቀመጥ ይቀላል - ሜታዳታ መሰብሰብና ማከማቸት እንደሚባለው። NSA ይህንን ያደርጋል - ከአለም ዙሪያ “ሜታዳታ” ይሰበስባል። ወገኖቹ አውሮፓውያን፣ ቀልደኞቹ ራሺያና ቻይና በእርግጥ NSA ሁሉንም አገራት አይሰልልም። በተለይ አፍሪካን ዞር ብሎ የሚያያት አይመስልም። እንኳን የአፍሪካ አገራትን ሊሰልል ይቅርና፣ የምስራቅ አውሮፓ አገራት ላይም እንኳ ብዙ ትኩረት አያደርግም። ዋነኛ ትኩረቶቹ፣ ቻይና፣ ሰሜን ኮሪያ፣ ኢራን፣ ሶሪያ፣ ፓኪስታንና አፍጋኒስታን የመሳሰሉ አገራት ናቸው - “ለአሜሪካ ደህንነት ስጋት ናቸው” በሚል።

በሁለተኛ ደረጃ ደግሞ፣ የምዕራብ አውሮፓ አገራት ላይ ያተኩራል - “የአውሮፓ ደህንነት ያሳስበኛል” በሚል። NSA በአውሮፓ አገራት ላይ ስለላ የሚያካሂደው ለወዳጅ አገራት ደህንነት በማሰብ እንደሆነ ቢገልፅም፣ በርካታ የአውሮፓ መንግስታት ቁጣቸውንና ቅሬታቸውን ሲገልፁ ሰንብተዋል። በእርግጥም፣ የጀርመኗ መራሄ መንግስት አንጌላ ሜርከልን ጨምሮ፣ በርካታ የአውሮፓ መሪዎችና ሚኒስትሮች ስልካቸው በNSA መጠለፉ አስገራሚ ነው። የራሺያ እና የቻይና መንግሰታትም በፊናቸው፣ አሜሪካን ለማጥላላት ጥሩ አጋጣሚ አገኘን ብለው ሲተቹ ከርመዋል። እንዲያም ሆኖ፣ የአውሮፓ ባለስልጣናት ቁጣና ቅሬታ፣ ከአስመሳይነት ተለይቶ እንደማይታይ የዘገበው ዎልስትሪት ጆርናል፣ ከቻይናና ከራሺያ የሚሰነዘረው ትችትም አስቂኝ እንደሆነ ይገልፃል። እንዴት በሉ። በኒው ዮርኩ የተባበሩት መንግስታት ተቋም የአውሮፓ ህብረት ተወካይ መስሪያ ቤትን በምሳሌነት መጥቀስ ይቻላል። NSA በአውሮፓ ህብረት መስሪያ ቤት ውስጥ የስለላ መሳሪያዎችን እንደተከለ የዘገበው ዎልስትሪት ጆርናል፣ “ይሁን እንጂ ቀድሞም ቢሆን ቦታው ከስለላ ነፃ አልነበረም” ብሏል። የNSA የስለላ ባለሙያዎች የአውሮፓ ህብረት ቢሮዎችን በስለላ መረብ ውስጥ ለማስገባት ሲሰማሩ ነው፣ ከነሱ ቀድሞ የቻይና መንግስት የስለላ መረብ መዘርጋቱን በአካል ያዩት። የራሺያ መንግስትም እንዲሁ፣ ለጂ20 ስብሰባ የመጡ የተለያዩ ፕሬዚዳንቶችንና ባለስልጣናትን ለመሰለልና ስልኮቻቸውን ለመጥለፍ የሚያስችል መሳሪያ ተጠቅሟል።

ታዲያ፣ ራሺያና ቻይና፣ ከዳር ሆነው ትችት መሰንዘራቸው የምን አስመሳይነት ነው? የአውሮፓ መንግስታት ሁኔታም ተመሳሳይ ነው። የአሜሪካ መንግስት፣ በአንድ ወር ውስጥ ከአራት ቢሊዮን በላይ የስልክ መረጃዎችን ከጀርመን እንደወሰደ የገለፁ ዘገባዎች፣ ከፈረንሳይና ከስፔንም በአንድ ወር ውስጥ ከመቶ ሚሊዮን በላይ የስልክ መረጃዎችን እንደሰበሰበ ገልፀዋል። ነገሩ እውነት መሆኑ በተለያዩ ምንጮች ቢረጋገጥም፤ የጀርመን፣ የፈረንሳይና የስፔን ባለስልጣናት በቁጣ ቅሬታቸውን ሲገልፁ መታየታቸው አስቂኝ ድራማነት ያለፈ ትርጉም የለውም። ለምን ቢባል፣ መረጃዎቹን ሰብስበው ለNSA የሰጡት የየአገሮቹ የስለላ ተቋማት ናቸው - NSA በፈንታው የራሱን መረጃ ያካፍላቸዋላ። እንዲህም ሆኖ፣ NSA ከዳር እስከ ዳር መረጃዎችን አፋፍሶ መሰብሰቡ ትክክል ነው ማለት አይደለም። የሰዎችን የግል ሕይወት ይዳፈራል። መግቢያ መውጪያ የሚያሳጣ የመንግስት ስለላ እርግጥ ነው፤ የአሜሪካ ብሄራዊ የፀጥታ ኤጀንሲ (NSA)፣ የዜጎችን የግል ሕይወት ይጥሳል በሚል የሚቀርብበትን ተደጋጋሚ ወቀሳ ከማስተባበል ተቆጥቦ አያውቅም። “የዜጎችን የስልክ ንግግርና የኢሜይል መልእክት እየጠለፍኩ አይደለም” የሚለው NSA፣ ሰዎችን በስም የማይጠቅስ የስልክ፣ የኢሜይል፣ የግዢ፣ የባንክ፣ የሐዋላ፣ የክፍያ ጥቅል መረጃዎችን (ሜታዳታዎችን) ማከማቸት የዜጎችን የግል ሕይወት አይጥስም ይላል።

ከየትኛው ቁጥር ለየትኛው ቁጥር እንደተደወለ፣ መቼ ተደውሎ ለምን ያህል ደቂቃ የስልክ ግንኙነቱ እንደቀጠለ የሚያሳዩ ጥቅል መረጃዎችን እንሰበስባለን እንጂ፣ የዜጎችን የስልክ ንግግር አንቀርፅም ብለዋል የNSA ዳሬክተር። በዚያ ላይ፣ “የተሰበሰቡትን መረጃዎች አከማቻለሁ እንጂ በዘፈቀደ መረጃዎቹን አልመረምርም፣ አልሰልልም” የሚለው NSA፤ መረጃዎቹን የምመረምረውና የምሰልለው የጥርጣሬ ፍንጮች ላይ በመመስረት ብቻ ነው ይላል። ካለፈው ሰኔ ወር ወዲህ በአውሮፓ እና በአሜሪካ ጋዜጦች የተሰራጩ ዘገባዎች ግን፣ ይህንን የNSA ማስተባበያ የሚቃረኑ ናቸው። NSA፣ “ፕሪዝም” እና “አፕስትሪም” በሚሉ የስለላ ፕሮጀክቶች፣ የስልክ ንግግሮችንና የኢንተርኔት ግንኙነቶችን በቀጥታ እየጠለፈ እንደሚሰልልና እየቀረፀ እንደሚያስቀምጥ ዘጋርድያን ዘግቧል። የየእለቱን መረጃ ሁሉ ሰብስቦ ለማስቀመጥ፣ በየእለቱ በሚሊዮን የሚቆጠሩ አዳዲስ ኮምፒዩተሮችን መግዛት እንደማይቻል ግልፅ ቢሆንም፣ ሌሎች ዘዴዎች አሉ።

ለምሳሌ፣ ከአሜሪካ ጋር በቅርበት ከሚሰሩ አራት አገራት መካከል አንዷ የሆነችው እንግሊዝ፣ የስለላ መረጃዎችን ለመጥለፍና ለማከማቸው ዘመናዊ ተቋም እየገነባች ነው። ተቋሙ ግዙፍ ከመሆኑ የተነሳ፣ በአውሮፓና በኤስያ አገራት ዙሪያ፣ በስልክና በኢንተርኔት የሚሰራጩ መልእክቶችን በሙሉ ለሶስት ቀናት ቀርፆ ማቆየት እንደሚችል የዘገበው ዘጋርዲያን፣ የ30 ቀናት ጥቅል መረጃዎችንም (ሜታዳታዎችንም) ሰብስቦ ማቆየት ይችላል ብሏል። እንግሊዝ እንዲህ ማድረግ ከቻለች፣ እጅግ ግዙፍ የሆነው የአሜሪካው NSA በብዙ እጥፍ የሚበልጥ የመረጃ ሰብስብ አከማችቶ ማቆየት እንደሚችል ለመገመት አይከብድም። (በነገራችን ላይ፣ ለአመታት ተደብቆ የቆየ ይሄ ሁሉ ሚስጥር፣ ድንገት በግላጭ የተዘረገፈው ለNSA በኮንትራት ይሰራ የነበረው ሮበርት ስኖደን ሰርቆ ባወጣቸው 50 ሺ ገደማ ሚስጥራዊ ደብዳቤዎች ሳቢያ ነው።) የስልክ፣ የኢሜይል፣ የግዢ እና የሽያጭ፣ የኪራይና የስጦታ፣ የጉዞ እና የጉብኝት መረጃዎች ላይ፣ የጐዳና ካሜራዎችና የጂፒኤስ፣ የሰው አልባ አውሮፕላንና የሳተላይት መረጃዎች ሲጨመሩበት፣ የዘመናችን ስለላ ምንኛ የሰዎችን የግል ሕይወት እንደሚያጠፉ ሲታሰብ ያስፈራል፡፡

            ከዕለታት አንድ ቀን፤ አንዲት አይጥ ወደ አያ ዝሆን ሄዳ ልጁን ለልጇ እንዲድርላት ጠየቀችው። አያ ዝሆንም፤ “እንዴት ባክሽ? እንዴት ብትደፍሪኝ ነው ልጄን ለልጅሽ የተመኘሻት?! እኔ ማን እንደሆንኩ አታውቂም ማለት ነው፡፡ ከእንስሳት ሁሉ ግዙፉና ጠንካራው እኔ ነኝ፡፡ ጥርሴ ልዩ ዋጋ ያለው አንጋፋ አባት ነኝ፡፡ የአንድ ሙሉ ጫካ ዛፍ ገለባብጬ ለመጣል እችላለሁ፡፡ እና ለአንድ አይጥ ለሚባል ጉድጓድ ውስጥ ለሚኖር ፍጡር፣ ለዚህ ደቃቃ ፍጡር ልጄን የምድር ይመስልሻል? ልጄንማ እንዲህ አድርጌ አላዋርዳትም!” አላት፡፡ አይጢትም፤ “ባለነጭ ጥርሱን ዝሆን ምንም ደቃቃ ብሆን የምጠቅመው ቀን ይመጣል” አለችው፡፡ አያ ዝሆንም በንቀት፤ “አንቺን ዓይነት ደቃቃ ለእኔ ዓይነት ግዙፍ እንስሳ ምን ሊያደርግ እንደሚችል አሁኑኑ ማወቅ እፈልጋለሁ፡፡

አለበለዚያ ስለ ድፍረትሽ እግሬ ሥር አስገብቼ እደፈጥጥሻለሁ!” እያለ ወደሷ መምጣት ሲጀምር፤ በድንገት አዳኝ - ፈረሰኞች እየጋለቡ አቧራውን እያስጨሱ መጡ፡፡ አያ ዝሆን እነዚህ የአደን ሰዎች፤ ያንን የሚኩራራበትን ነጭ ጥርሱን ፍለጋ ሊገድሉት እንደሚችሉ በመገመት መደበቂያ ቦታ ይፈልግ ጀመር፡፡ ይሄኔ አይጢቱ፤ “ጌታ ዝሆን! አይዞህ አትፍራ፡፡ አሁን እየመሸ በመሆኑ ጠላቶችህ አያዩህም፡፡ እኔ ግን ችሎታዬን አሳይሃለሁ” አለችው፡፡ “እሺ” ብሎ ጥግ ይዞ ቆመ፡፡ ዕውነቱም ፈረሰኞቹ ስለመሸባቸው በአካባቢው ፈረሶቻቸውን አስረው ተኙ፡፡ ጨለማው ዐይን ሲይዝ አይጢት ሥራዋን ጀመረች፡፡

የኮርቻውን ቀበቶ፣ የድሃራይና ቀዳማይ ማንገቻ፣ የመቀመጫውን ግላሥ፣ የእርካቡን ገመድ፤ በጥርሷ ቀረጣጠፈችው፡፡ ፈረሰኞቹ፤ ጠዋት ፈረሳቸው ላይ ወጥተው አደናቸውን ሊቀጥሉ ሲጋልቡ ኮርቻና እርካባቸው ተበጣጥሶ እየተንሸራተቱ ወደቁ፡፡ እግርና እጃቸው ተሰብሮ አደናቸውን አቋረጡ፡፡ አያ ዝሆን ዛፉን ተደግፎ፣ በአይጢቱ ሥራ ተደንቆ፣ “ዕውነትሽን ነው እመት አይጥ፡፡ ከእኔ ጥርስ ያንቺ ጥርስ እንደሚሻል ገባኝ፡፡ ለትልቁ እንስሳ ትንሿ እንስሳ ልትጠቅመው እንደምትችል አስተዋልኩ፡፡ “በቃ ልጄን ለልጅሽ እድርለታለሁ” አላት፡፡

                                                       * * *

ትልቅ ነን የምንል ሹሞች፤ ባለሥልጣናት ወይም የበላይ አካላት፤ ትናንሾች ናቸው ብላችሁ የምታስቧቸውን የበታች አካላት አትናቁ! ትንሹም አቅም አለውና፡፡ አበሻ ጋን በጠጠር ይደገፋል ይላል! ጋን በክብ መቀመጫው ለመቆም ምን ያህል እንደሚቸገር መረዕየት (Visualize የማድረግ) አቅም ብቻ ነው የሚጠይቀው፡፡ በፓርቲ ሰውነት፤ በመንግሥት ሹመኛነት፣ በትምህርት “ማዕረግ”፣ በውትድርና የበላይነት፣ በሊቀመንበርነት ነጭ ጥርስ ያለን ግዙፍ አካል ነን ለማለትና ለመገበዝ መሞከር፤ ክፉ ቀን ሲመጣ የት ልደበቅ ማለት ምን ያህል እንደሚያሸብር የትልቁ ዝሆን ታሪክ ሁነኛ ነገር ነው፡፡ ላፎንቴን ገጣሚው፤ “ድርጭትና ተራራው” በሚለው ግጥሙ - “ይህ ኩራትና ግብዝነት፣ መቼም የትም አያደርስህ እንዳንተ ትልቅ ባልሆንም፤ እንደኔ ትንሽ አደለህ!” የሚለው ይሄንኑ ዕውነታ ለማፀህየት ነው፡፡ ተፎካካሪዎችን መናቅ፣ ተቃዋሚዎችን መናቅ ከግዝፈት እሳቤ የመጣ ከሆነ ራስን ያለማየት ችግር እንዳለ ነው የሚያስገነዝበን፡፡ ወጣት ልጆቻችን የትምህርት ድጋፍ እንደሚያስፈልጋቸው አጠያያቂ አይደለም፡፡

ትምህርት ተማሩ የሚባለው የሚማሩበት ከባቢ አየር ጤናማ ሲሆን ነው፡፡ የትምህርቱ ጥራትና ክብደት፣ መምህሩ፣ የጽዳት ሠራተኞቹ፣ የትምህርት መሣሪያዎቹ፣ የመጫወቻ ሜዳዎቹ እና የመጫወቻ ክፍለ ጊዜያቱ፣ የማጠናከሪያ ትምህርቱ፣ የወላጅ መምህርና ተማሪ ስለስተ ጥምረቱ፡፡ ዛሬ ጥያቄ ውስጥ ነው፡፡ አንዱ ሲሳካ ሌላው እያነከሰ ወላጆችን እያስጨነቀ ነው፡፡ ከዚህ ሁሉ በላይ ግን ተማሪዎች ከትምህርት ገበታቸው ሸፍተው የሚውሉባቸው ቦታዎች እጅግ ዘግናኝ ገጽታ ነው ያላቸው፡፡ ያለዕድሜያቸው በሱስ ይጠመዳሉ፡፡ ያለ ዕድሜያቸው ያልተፈለገ እርግዝና ሰለባ ይሆናሉ።

ት/ቤቱም ወላጁም የዚህ ዕውቀት የለው አይመስሉም፡፡ ስለተረካቢ ትውልድ የምናስብ ከሆነ ይህን አሰቃቂ ዕውነታ ተቀብለን አስፈላጊውን እርምጃ መውሰድ አለብን! ዛሬ የማይናገር አፍ፣ ራስ - አቀብ (Self –censored) አፍ፣ የፈራ አፍ እንዳለ ሁሉ፤ ቀን አመቸኝ ብሎ የሚቀላምድ አፍ፤ የባለቤቱ ልጅ ነኝ ብሎ ዘራፍ የሚል አፍ፣ እኔ ብቻ ነኝ የተማርኩ የግድህን ስማኝ የሚል አፍ፤ የሚሰማውና የሚታዘበው አድማጭ ያለ የማይመስለው ዋልጌ አፍ ብዙ አፍ አለ፡፡ ህገመንግስት በዘፈቀደ የሚተረጐም ከሆነ፤ ቅጡን ያጣና አፍራሹና ፈራሹ የማይታወቅበት ሥርዓተ አልበኝነት እንዳይፈጠር ሥራዬ ብሎ ማጤን ተገቢ ነው፡፡ ህገ -መንግሥት አላዋቂ የሚጭበረበርበት፤ ጮሌ እንዳሻው እኔን ብቻ ስሙ የሚልበት መሆን የለበትም፡፡

የመመሪያዎች ግልጽነት ህብረተሰብን ከመወናበድ እንደሚያድን አንድ ሁለት የለውም። ወቅታዊ መግለጫዎች ራስ - አድን በመሆናቸው ይበረታታሉ፡፡ መንገድ እንደሚዘጋ ያወቀ አሽከርካሪ ካልሆነ ወጪና የጊዜ ኪሣራ ይድናል፡፡ ሚዲያዎቻችን ወቅታዊ መረጃ ማቅረብ ግዴታቸው ሆኖ ሳለ በሌሎች ዜናዎችና ዘገባዎች ከተጠመዱ “ጅብ ከሄደ ውሻ ጮኸ” እንዳይሆኑ ሥጋት አለ፡፡ ሁኔታዎች ተባብሰው የማይቀለበሱበት ደረጃ እስኪደርሱ መጠበቅ ቢያንስ የዋህነት ነው አንተ ነህ አንተ ነህ በሚል ሰበብ መሸጋገር የአፍታ ጠቀሜታ ብቻ ነው ያለው፡፡ ጥቅም ያለው ነገር ሲሆን ራስን ማጨት፤ የከፋ ነገር ሲመጣ ሌላውን መመደብ፤ ቢያንስ ጊዜ ያለፈበት ታክቲክ እንደሆነ እንረዳ፡፡ “በሌላ ሰው እጅ እሳት መንካት አያስፈራም!” የሚለውን ተረት የአዘቦቱ ሰውም ይረዳዋል፡፡

               የኢትዮጵያ አየር መንገድ ካዘዛቸው አራት ግዙፍ ቦይንግ 777300ER አውሮፕላኖች የመጀመሪያውን ትናንት የተረከበ ሲሆን፤ ለቦይንግ አውሮፕላኖች የሚያገለግሉ የኤሌክትሪክ መስመሮችን መፈብረክ ይጀምራል ተባለ፡፡ አየር መንገዱ በበረራ ታሪኩ 400 ሰዎች የመያዝ አቅም ያለው አውሮፕላን ሲረከብ የመጀመሪያው ሲሆን፣ አውሮፕላኑ ብዙ መንገደኞችን ለማስተናገድ እንደዋሽንግተን ዲሲ፣ ዱባይና ጉዋንዙ (ቻይና) የመሳሰሉ በተጨማሪ ረዥም ርቀት ያለማቋረጥ መጓዝ እንደሚችል ታውቋል፡፡

በአለም በግዝፈታቸው በሚታወቁና በጄኔራል ኤሌክትሪክ ኩባንያ የተሰሩ ኢንጂነሮች የሚንቀሳቀሰው ይሄው አውሮፕላን፣ በአራት ረዣዥም ክፍሎች በሦስት ረድፍ የተሳፋሪ መቀመጫዎች ሰትሮ የያዘ ነው፡፡ መቀመጫዎቹ ምቹ፣ ቦታው ሰፊና ጣሪያው ከፍ ያለ ነው፡፡ የአውሮፕላኑ አብራሪ ካፒቴን ካሌብ ማሞ፣ ሲያትል ከሚገኘው የቦይንግ ኩባንያ ማዕከል እስከ ቦሌ አውሮፕላን ማረፊያ ለ15 ሰዓታት በመብረር መድረሳቸውን ገልፀው፤ አውሮፕላኑ ዘመናዊ ከመሆኑም በላይ በዘመኑ የቴክኖሎጂ ውጤቶች የተፈበረከ ስለሆነ ለመንገደኞች ከፍተኛ እንደሚሰጥ ተናግረዋል፡፡ የአሜሪካ አምባሳደር ፓትሪሺያ ሃሳላክ በበኩላቸው የቦይንግ እና የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግንኙነት ጠንካራ መሆኑን በመጥቀስ፣ አየር መንገዱ ለቦይንግ አውሮፕላኖች የሚያገለግሉ የኤሌክትሪክ መስመሮችን መፈብረክ እንደሚጀምር ተናግረዋል፡፡

ዛሌፍ የሥነ ጥበብ እና ፋሽን ዲዛይን ተቋም፣ በታዋቂ ዲዛይነሮች የተሰሩ አልባሳት የተካተቱበት የፋሽን ትርዒት ዛሬ ከቀኑ 10 ሰዓት በኢንተርኮንቲነንታል ሆቴል እንደሚያቀርብ አስታወቀ፡፡
ከተቋሙ የሥራ ውጤቶች መካከል በ2003 ዓ.ም በአዲስ አበባ ሂልተን የቀረበው በኮንዶም የተሰሩ አልባሳት ዐውደርዕይ ይገኝበታል።

 

Saturday, 02 November 2013 11:54

ወፍ እና ማለዳ

እንኳንስ ችግኙ፣ ሰዎች የተከሉት
ሥር ይይዝ ነበረ፣ አዕዋፍ የዘሩት፡፡
ዘንድሮ ግን ወፎች፣ እንኳንስ ሊዘሩ
ናፍቆኛል ማለዳ፣ መስማት ሲዘምሩ፡፡
ወፎች ከማለዳ
በምን ተቃቃሩ?
ፅልመቱ ሲገፈፍ
እንዳላበሠሩ፤
ማዜም ተስኗቸው
ተዘግቶ ጀንበሩ
ወደሚነጋበት
ወዴትስ በረሩ?!

እችልሻለሁ!!
ስለ እውነት እልሻለሁ፣
ስለወደድኩሽ እችልሻለሁ!
የአያሌ ሞገደኞች ድምር፣ በአንድነት ተጨፍልቆ
ከሰብእናሽ ተላቁጧል፤ አድርጎሻል የሴት ኅልቆ፡፡
ካልተገሩ ባህርያት፣ እስከጠፋ ያለም ፍጥረታት
ነፍስያና አመላቶች ተጎንጉነው ያየሁባት
ብትሆኚም ብቸኛዋ፣ እስከዛሬ ያፈቀርኳት
እልሻለሁ “አያሌዎች”፣ ምስክር ነኝ ስለ እውነት!
ይህም ቢሆን … “እችልሻለሁ!”
ባንዲት ነፍሴ እምላለሁ!
ፍቅር ቀድሞ ገሎኛል፣ ስለምንስ እፈራለሁ?
የምታደርጊውን አድርጊኝ፣ ይኸው ፊትሽ ቆሜያለሁ
(“ሀ-ሞት” ከተሰኘው
የሄኖክ ስጦታው የግጥም መድበል
የተወሰደ - 2005)

                  የመንግሥት ተቋማት አገልግሎት አሰጣጥን በተመለከተ ተደጋጋሚ የነዋሪዎች እሮሮዎችና አቤቱታዎች ሲስተጋቡ የቆዩ ሲሆን መንግስት የአገልግሎት አሰጣጡን ለማቀላጠፍ፣ የስነምግባር ጉድለቶችን ለማሻሻል የተለያዩ እርምጃዎች መውሰዱ ይታወቃል፡፡ ሆኖም ግን አሁንም ችግሮቹ እንዳልተፈቱ ብዙዎች ይናገራሉ፡፡ ባለፈው ሰሞን የማህበራዊ ጥናት መድረክ “የህዝብ አገልግሎት አሰጣጥ ስነምግባርና ተጠያቂነት” በሚል ርዕስ በግዮን ሆቴል ዎርክሾፕ አዘጋጅቶ ነበር፡፡ በዎርክሾፑ ላይም የቀድሞ ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽነርና አሁን በግል አማካሪነት የሚሰሩት አቶ አትክልት አሰፋ እና የቀድሞ ሲቪል ሰርቪስ ጀነራል ዳይሬክተርና አሁን በግል ስራ ላይ የተሰማሩት የህግ ባለሙያ አቶ መስፍን ታፈሰ እንዲሁም የማህበራዊ ጥናት መድረክ ስራ አስፈፃሚ ዳይሬክተር፣ ዶክተር ምህረት አየነው የቀረበውን ፅሁፍ የሚተች ዳሰሳ አቅርበዋል፡፡
ኢትዮጵያ አስራ አራት የመንግሥት አገልግሎት ማሻሻያ ፕሮግራም እንዳላትና ሁሉም ፕሮግራሞች አገር በቀል እንደሆኑ የገለፁት አቶ አትክልት አሰፋ፤ ዋናው ፕሮግራም የመንግስት አገልግሎት (ሲቪል ሰርቪስ) ማሻሻያ እንደሆነ አስረድተዋል። በአገልግሎት አሰጣጥ ላይ ለውጥ ለማምጣት የሚያስችሉ ተቋማት መቋቋማቸውን፤ የተለያዩ የህግ ማእቀፎችም መዘጋጀታቸውን አቶ አትክልት ጠቁመዋል፡፡ ችግሮች ቢኖሩም ትልቅ ለውጥ መታየቱን የተናገሩት አቶ አትክልት፤ የሙስናውም ደረጃ በንፅፅር ሲታይ በዝቅተኛ ደረጃ ላይ መሆኑን ጠቁመው፤ በተለያዩ የአገልግሎት ዘርፎች የሚስተዋሉ የስነምግባር ጉድለቶች እና ግድፈቶችን ዘርዝረዋል፡፡
በመጀመሪያ የተዳሰሰው የትምህርት ዘርፍ ሲሆን በፈተና እና በውጤት አሰጣጥ ላይ የሚፈፀሙ ማጭበርበሮች፣ ጉቦ መቀበል፣ የሀሰት ትራንስክሪፕትና ሰርተፊኬት መስጠት፣ የመምህራንን እድገት እና ዝውውር ከጥቅም ጋር ማያያዝ፣ ሴት ተማሪዎችን ለወሲብ ማስገደድና የመምህራን ለግል ስራ ቅድሚያ መስጠት እንዲሁም በስራ ገበታ ላይ አለመገኘት የሥነምግባር ጉድለቶች ተብለው ተጠቅሰዋል፡፡ በጤና ዘርፍ ደግሞ ለኤክስሬይ እና ለቀዶ ጥገና አገልግሎቶች ጉቦ መጠየቅ፣ የሆስፒታል አልጋ በጉቦ ወይም በዝምድና እንዲሰጥ ማድረግ፣ ለታካሚዎች ተገቢውን እንክብካቤ ያለማድረግ፣ የባለሙያ የብቃት ማነስ፣ የመድሀኒት እና የአምቡላንስ አቅርቦት ያለመኖር፣ አላስፈላጊ ምርመራዎችን በማዘዝ ታካሚዎችን ላላአስፈላጊ ወጪ መዳረግ፣ ታካሚዎችን ወደ ግል ፋርማሲ እና ክሊኒኮች መላክ፣ ተቆጣጣሪን በጉቦ መደለል እና የማጭበርበር ድርጊት መፈፀም፣ መገልገያ ቁሳቁሶችን መስረቅ እና ፈንድ ያለ አግባብ መጠቀም እንደ ጉድለት ቀርበዋል፡፡
አቶ አትክልት፤ ፍርድ ቤቶች፣ አቃቤ ህጎችና ፖሊስ ዘንድ ይፈፀማሉ ያሏቸውን የስነምግባር ጉድለቶችም በዳሰሳቸው ዘርዝረዋል፡፡ ከእነዚህም መካከል፡- ፍርድ ቤቶች እና አቃቤ ህጎች ውሳኔን ለማስቀረት ወይም ለመጀመር ጉቦ መጠየቅ ወይም መቀበል፣ የአቃቤ ህጎች ስልጣናቸውን በመጠቀም ክሶችን መግደል ወይም ነፍስ እንዲዘሩ ማድረግ፣ ክስን በአግባቡ ያለመያዝና በፍትህ አስተዳደሩ ላይ የሚታዩ መጓተቶች፣ የብቃት ማነስ እና ጉቦ በመቀበል ክስን ማቅለል… የሚሉት ይገኙባቸዋል። የፖሊሶችን የስነ ምግባር ጉድለቶች ሲጠቅሱም፤ እስረኞችን በአግባቡ ያለመያዝ፣ የትራፊክ ፖሊሶች ህገወጥ ሾፌሮችን በጉቦ ማሳለፍ እንዲሁም በፀጥታ ጥበቃ ላይ የተሰማሩ ፖሊሶች በጥፋት መጠየቅ ያለባቸውን በጥቅም በመደለል አለመጠየቅ፣ ማስረጃዎችን ለማድበስበስ ምስክሮችን እንዳይቀርቡ ማድረግ… የሚሉትን ዘርዝረዋል፡፡
በንግድና ኢንቨስትመንት ከሚስተዋሉ የስነምግባር ጉድለቶች ውስጥም ህገወጥ ፈቃድ መስጠት፤ በህገ ወጥ፣ ደረጃቸውን ባልጠበቁና ጥራታቸው በተጓደለ ምርቶች ላይ የሚደረግ ክትትልና ቁጥጥር የይስሙላ መሆን፣ የሸቀጦች እጥረት ላይ የሚደረግ ቁጥጥር ማነስ የተጋነነ የዋጋ ማሻቀብ እና የውድድር መንፈስን በሚቃረኑ እና ከእውነት በራቁ የሸቀጦች ማስታወቂያ ላይ የሚደረጉ ቁጥጥሮች ማነስ በጥናቱ ላይ ተጠቅሰዋል፡፡
ከመሬት ጋር በተያያዘ የሚፈፀሙ የስነምግባር ጉድለቶችን በተመለከተ ደግሞ በቤት ልማት ላይ የተሰማሩ ባለሀብቶችን በቦታ አሰጣጥ ላይ በእኩል አይን አለማየት፣ የተጭበረበሩ የመሬት ባለቤትነት ሰርተፊኬትና ሰነድ አዘጋጅቶ መስጠት የሚሉት በዋናነት የስነምግባር ጉድለቶች ተብለው ተቀምጠዋል፡፡
የመንግስት ቤቶችን አስመልክቶም፤ ቤት ያለጨረታ ማከራየት፣ በኪራይ አሰባሰብ ላይ የብቃት ማነስና መዘግየት፣ በህገወጥ መንገድ ቤት በያዙና በተከራይ አከራይ ጉዳይ ላይ የክትትል ማነስ፣ ከህግና ደንብ ውጭ መስራት፣ በኪራይ ተመን ላይ ወጥ ያለመሆን እና የተቀናጀ የመረጃ ዘዴ ያለመኖር… የተጠቀሱ ሲሆን፤ በአገልግሎት ዘርፍም የእቃ ግዢና አቅርቦት ችግር፣ ተደጋጋሚ የመብራት እና የውሀ መጥፋት፣ የዘገየ የስልክ ጥገና እና ቀርፋፋ የኢንተርኔት አገልግሎት ጉድለት ተብለው ተዘርዝረዋል፡፡
የኮንስትራክሽን ዘርፉም ከስነምግባር ጉድለቶች አላመለጠም - በአቶ አትክልት ዳሰሳ መሰረት፡፡ ግንባታዎችን ማጓተት፣ ጥራቱን ያልጠበቀ ግንባታ መቀበል፣ የዋጋ መዛባት፣ በኮንትራክተሮች እና በሱፐርቫይዘሮች መካከል የሚደረግ መመሳጠር፣ ላልቀረቡ እቃዎች ክፍያ መፈፀም፣ ብክነት፣ ስርቆት እና አግባብ ባልሆነ መንገድ ተጫራቾችን መለየት የሚሉ ይገኙበታል፡፡
የቤቶች ልማት ፕሮጀክት ላይ የሚታዩ የሥነምግባር ጉድለቶችን የዳሰሱት አቶ አትክልት፤ ህግን ባልተከተለ መንገድ ያለ እጣ ለነዋሪዎች ቤት መስጠት፣ ባልና ሚስትን የሁለት ቤቶች እድል ተጠቃሚ ማድረግ፣ የከተማዋ ነዋሪ ያልሆኑና ያልተመዘገቡ ሰዎችን ተጠቃሚ ማድረግ እና በርክክብ ላይ የሚታይ መዘግየትን ጠቅሰዋል፡፡ ለቀበሌ እና የወረዳ ተመራጮች
የሚሰጣቸው የቅድሚያ የቤት እድል፣ ብቃት የሌላቸውን ሰዎች ለስራ መመልመል፣ የነዋሪነት የቀበሌ መታወቂያና ሰርተፊኬት በጉቦ መስጠት፣ የገንዘብ ብክነት፣ በህገወጥ የቤቶች ግንባታ ላይ ወቅታዊ ቁጥጥር እና እርምጃ ያለመውሰድ እንዲሁም በስብሰባዎች መብዛት ሳቢያ የጊዜ አጠቃቀም ላይ የሚፈጠሩ ችግሮች ተዘርዝረዋል፡፡
ቀደም ሲል በብቃቱና በቅልጥፍናው የሚታወቀው ኢሚግሬሽን፤ በአሁኑ ወቅት ፓስፖርት ለመስጠት ረጅም ጊዜ እንደሚወስድበት የተጠቀሰ ሲሆን መንግስታዊ ባልሆኑ ድርጅቶችና በሲቪል ማህበራት ላይ ጠበቅ ያለ ቁጥጥር እንደማይደረግም አቶ አትክልት በጥናታቸው ገልፀዋል፡፡
በጥናቱ ላይ ትችት ያቀረቡት አቶ መስፍን በበኩላቸው፤ የስነምግባርና የአገልግሎት አሰጣጥ ማሻሻያ ፕሮግራሙ ዲዛይን ከጊዜ ጋር የመራመድ ሁኔታው ምን ይመስላል? ትግበራውስ ምን አይነት ቅደምተከተል የያዘ ነው? በማሻሻያ ፕሮግራሙ ላይ የሰው ሀይሉ ሚና ምን ይመስላል? ቢፒአር ምን ያህል ከፖለቲካ የፀዳ ነው? ውጤታማ ነው ሲባል ውጤቱ እንዴት ይለካል? የሚሉ ጥያቄ አዘል ትችቶችን ሰንዝረዋል፡፡
ዶክተር ምህረት ደግሞ ትኩረት ያደረጉት በጥናታዊ ፅሁፉ ጎልተው መውጣት አለባቸው ባሏቸው ነጥቦች ላይ ነው፡፡ በመንግስት አገልግሎት አሰጣጥ ስነምግባር እንዲሰፍንና ተጠያቂነት እንዲጎለብት በሙያው የዳበረ፣ ነፃና በችሎታው ብቻ የተመረጠ የመንግስት ሠራተኛ ወሳኝ ነው ብለዋል። “ሰራተኛው ከፓርቲ ወይም ከፖለቲካው ቁጥጥር ነፃ ሆኖ በሙያው የተካነና ለሀላፊነቱ ተጠያቂ ቢሆን አብይ መስፈርት ነው ብዬ አስባለሁ” ብለዋል፡፡ “የስነ ምግባር ወይም የአፈፃፀም ጉድለቱን በፓርቲ ጥላ ስር መደበቅ ያለበት አይመስለኝም፡፡ በሙያው ይፈረጃል፤ ይመለመላል፣ ያድጋል፣ ይደራጃል፡፡” ሲሉም አብራርተዋል፡፡
ነፃ የሆነና በሙያው የተካነ ጋዜጠኛና ሚዲያ መኖር ዋነኛ የፖሊሲ ጥያቄ እንደሆነም ዶ/ር ምህረት ተናግረዋል፡፡ ተንቀሳቅሶ ማንቀሳቀስ የሚችል ሲቪል ማህበረሰብ ያስፈልጋል፤ ይሄ ጎላ ብሎ መውጣት አለበት ያሉት ዶ/ሩ፤ ነፃና ጠንካራ የሙያ ማህበራት ያስፈልጋሉ ብለዋል፡፡ “ዎች ዶግ” ተቋማት ነፃ ሆነው በህግ መሰረት መጠናከር እንዳለባቸውም ገልፀዋል። “ማሻሻያው” ብዙ ነው፤ የአንዱ ጥቅምና ጉዳት ሳይታይ በላዩ ላይ መደረብ ጉዳት አለው” ብለዋል - ዶ/ር ምህረት ባቀረቡት ጥናት፡፡

አንድ አዋቂና አስተዋይ የተባ ለመምህር ተከታዮቹን ይዞ ረዥም መንገድ ይሄድ ነበር ይባላል፡፡ በመንገዳቸው ላይ አንዲት የታሠረች ጥቁር ላም ይመለከታል፡፡ ከዚያም ወደ ተከታዮቹ ዞሮ፤
“የዚችን ጥቁር ላም ወተት መጠጣት ውጉዝ ነው!” አለ፡፡
ተከታዮቹ በአንክሮ አዳመጡት፡፡ መንገዳቸውን ቀጠሉ፡፡ ወደ አንድ መንደር ሲደርሱ፤ እኔ እዚህ አድሬ አረፍ ልበል፤ እናንተ ደግሞ ወደየመንደሮቻችሁ ተጠግታችሁ እደሩና ጠዋት ከዚሁ መንገድ እንቀጥላለን አላቸው”
ሁሉም ወደሚያድሩበት ሄዱ፡፡
በየደረሱበት ግን ለሰው ትምህርት ለመስጠት ሞከሩ፡-
“የጥቁር ላም ወተት ውጉዝ ነው እነዳትጠጡ” እያሉ አስተማሩ፡፡
ህዝቡም
“ይህንን ማን አለ?” ሲል ጠየቀ፡፡
“መምህራችን!” አሉት፡፡
ጥቁር ላም ያለው ሰው ሁሉ ከፊሉ አዘነ፡፡ ከፊሉ ግራ ተጋባ፡፡ ከፊሉ “መምህርን መጠየቅ አለብን፡፡ አንድ ደሀ ሰው ያለችው አንዲት ጥቁር ላም ብቻ ብትሆንስ? በምኑ ይኖራል?” ሲል አጉረመረመ፡፡
በነጋታው መምህሩ በመንደራቸው ሲያልፍ፣ “መምህር ሆይ የጥቁር ላም ወተት መጠጣት
ስለምን ተከለከለ፣ ስለምንስ ውጉዝ ነው አልክ?” ሲሉ ጠየቁት፡፡
መምህሩም፤
“ተከታዮቼ የጥቁር ላም ወተት መጠጣት የተወገዘ ነው” ብለዋችሁ ከሆነ ተሳስተዋል፡፡ እኔ ያልኩት ነገር የሚመለከተው፣ ትላንት መንገድ ላይ ያየናትን ጥቁር ላም ነው” አላቸው፡፡
ሰዎቹም “ያቺንስ ጥቁር ላም ምን የተለየ ነገር ብታይባት ነው? አሉና ደግመው ጠየቁት፡፡
“መልካም ጥያቄ ነው፡፡ ተከታዮቼም ይህን ጥያቄ ሊጠይቁኝ ይገባ ነበር፡፡ ያቺ ጥቁር ላም እበረት ውስጥ ታስራለች፡፡ ምንም ምግብ አይሰጥዋትም፡፡ ሆኖም ጠዋት ማታ ያልቧታል፡፡ ይሄ ተግባር ግፍ ነው፡፡ ወተቱም ከግፍ የተገኘ ወተት ይሆናል፡፡ ውጉዝ ነው ያልኩት ለዚህ ነው፡፡ የጥቁርዋ ላም ምሳሌነቱ በግፍ ለተገኘ ማናቸውም ገንዘብ ንብረትና ሀብት ሁሉ ነው!” ሲል አብራራላቸው፡፡
* * *
ነገርን በጅምላው መውሰድ ስህተት ላይ ይጥለናል፡፡ የዓለምን ተመራማሪዎች ሲያጣሉና ተከታዮችንም ሲያወዛግቡ የኖሩ አያሌ ጥያቄዎች ከትርጓሜ ስህተት የመጡ እንደሆኑ አንዘንጋ፡፡ በእኩይ መንገድ የተገኘ ማናቸውም ዓይነት ብልፅግና ያስጠይቃል ፡፡ ሊያስጠይቅ የሚችልን ማናቸውም ኢፍትሐዊ ነገር የፈፀመን አለቃም ሆነ ምንዝር፤ ባለሥልጣንም ሆነ ተከታይ ጉዳዩን አብራርቶ እንዲጠይቅ ማድረግ የተበዳይ መብት ነው፡፡ ላሚቱ ራሷም ተዟዙራ የምትበላው እንዳትፈልግ አስረን ስናበቃ ያልሰጠነውን ለመቀበል፣ ያልመገብነውን ለማለብ መፈለግ፣ የሚገኘውን ወተት የግፍ ንብረት እንደሚያደርገው ማስተዋል ዋና ጉዳይ ነው፡፡ የበታቾቻችን፣ ተከታዮቻችን፣ ካድሬዎቻችን በየደረጃው ለመርሆች፣ ለመመሪያዎችና ለራዕዮች የሚሰጡት ትርጓሜ የተሳሳተ ከሆነ፤ የሚሳሳተው ብሎም የሚጎዳው፣ አገር ሙሉ ሰው ነው፡፡ ስህተቱ እጅግ የከፋ የሚሆነው ደግሞ የሚሰጠውን መግለጫ ህዝብ አብራሩልኝ ሲል “እኔ ያልኩህን ብቻ ተቀበል” የምንል ከሆነ ነው፡፡ አንድም ያለዕውቀት አንድም በዕብሪት፣ ይህን ግትርነት ካሳየን አስከፊ ጥፋት ከመሆን አይዘልም፡፡ የመንግሥት ሠራተኛም ቢሆን የህዝብ አገልጋል እንጂ ገዢ ነኝ የሚል አስተሳሰብ ካለም አደገኛ ነው! አገርና ህዝብን መበደል ነው፡፡ ዋና ዋና መርሆቻችንና የፖለቲካ አቋሞቻችንን ከመመርመርና ቆም ብለን ከማየት ይልቅ በደመ-ነብስ መከተልና እንደቦይ ውሃ አብሮ መፍሰስ ከዚያም ይልቅ የበለጠ መጮህ፤ ቢያንስ የዋህነት ነው፡፡
አሌክሳንደር ፓፕ የተባለው ገጣሚ “በጭፍኑ መስማማት መዋሸት ነው” ይለናል /To blindly comply, is to lie/፡፡
በሀገራችን ተጠይቀው ያልተመለሱ፤ ተመልሰው ያላጠገቡ፤ ከናካቴው ያልተጠየቁ ወይም ለመጠየቅ የሚፈሩ፤ በርካታ የፖለቲካም፣ የኢኮኖሚም፣ የማህበራዊም፣ የባህልም ጥያቄዎች በልማድ ታጅለው ብዙ ጊዜ አልፏቸዋል፡፡ አንዳንዶቹ፤ ብንጠይቅ ማን ይመልስልናል በሚል ሰበብ፣ እንደተዳፈኑ የሚቀሩ ናቸው፡፡ አንዳንዶቹ ብንጠይቅ እንጠየቃለን በሚል ፍርሃት የሚዳፈኑ ናቸው፡፡ ጥቂቶቹ መጠየቅ እንዳለባቸው ሳናውቅ እንደቀለጡ የሚቀሩ ናቸው፡፡ አብዛኞቹ በምን ያገባኛልና በምን-ግዴ፣ ቸልታ የተሸፋፈኑ ናቸው፡፡ ዞሮ ዞሮ ሁሉም ጉዳት ሲያደርሱብን ማየታችን አልቀረም፡፡ በተናጠል የምናብጠለጥላቸውና የምንሸሙርባቸው፤ እንዲሁም በንቀት የምናንጓጥጥባቸው ግን፤ ሲደርሱብን እሪ የምንልባቸው፤ በርካታ የዕለት-ጉርስ የዓመት-ልብስ ተኮር አንገብጋቢ ጥያቄዎች እንደ ዐባይ ከዓመት ዓመት ይፈስሳሉ፡፡
“ከበሮ የተደለቀውን ያህል ይጮሃል” የሚለው ተረት፤ የመቺውን እንጂ የተመቺውን ድምፅ የማያስተጋባበት ሁኔታ ውስጥ ከሆነ ያለነው፣ የትርጓሜ ስህተት አለ ማለት ነው፡፡ ያ ደግሞ የጥቁሯን ላም ያህል አሳሳቢ ችግር ሆኖ እናገኘዋለን፡፡ የበደሉንን ይቅር ማለት ብቻ ሳይሆን መጠየቅም መልካም ሥነ-ምግባር ነው! የከበሮ መቺውንም፣ የተመቺውን ከበሮም፣ ነገር ለማወቅ የጠያቂነት ባህል እናዳብር!!