Administrator

Administrator

የተባበሩት አረብ  ኤሚሬቶች ንብረት የሆነው “ዲፒ ወርልድ ኩባንያ” የሚያስተዳድረው የበርበራ ወደብ፣ የኢትዮጵያን 30 በመቶ ጭነት እንዲያስተናግድ የሶማሌላንድ ባለሥልጣናት ማቀዳቸው ተነገረ፡፡
በዚህም መሰረት የወደብ አጠቃቀምና የጉምሩክ ሥርዓቶችን የተመለከተ ስምምነት በኢትዮጵያና ሶማሌላንድ መካከል መፈረም እንዳለበት የተገለጸ ሲሆን፤ ስምምነቱ በሚቀጥሉት 60 ቀናት ተጠናቅቆ  ሊፈረም እንደሚችል የሶማሌላንድ የወደቦች አስተዳደር አስታውቋል፡፡
የአስተዳደሩ ዋና ዳይሬክተር ሰኢድ ሃሰን አብዱላሂ በሰጡት ማብራሪያ፤ “ኢትዮጵያ ጎረቤታችን ናት፤ አብረን  ቢዝነስ መሥራት እንፈልጋለን። በአሁኑ ወቅት የወደብ አጠቃቀም ስምምነት እያዘጋጀን ነው። አንዴ ስምምነቱን ከተፈራረምን በኋላ፣ በመጀመሪያው ዓመት ከኢትዮጵያ ጭነት 30 በመቶውን እናስተናግዳለን” ብለዋል።
ከጥቂት ወራት በፊት እ.ኤ.አ. ጥር 1 ቀን 2024 ዓ.ም ኢትዮጵያና ሶማሌላንድ የተፈራረሙት የመግባቢያ ስምምነት በተመሳሳይ ወደ ተግባር የሚገባበት የመጨረሻው ስምምነት በ2 ወራት ገደማ ውስጥ ይጠናቀቃል ተብሎ እንደሚጠበቅም  የሶማሌላንድ ባለሥልጣናት ጠቁመዋል፡፡
የመግባቢያ ስምምነቱ ከተፈረመ በኋላ ውይይቶች ሲደረጉ መቆየቱን ያመለከቱት  ባለሥልጣናቱ፤ የቴክኒክ ኮሚቴዎች መዋቀራቸውንም ተናግረዋል። የመግባቢያ ስምምነቱ  ከመጨረሻው ሂደት ላይ ደርሶ ወደ ተግባር ከተገባ ኢትዮጵያ በሶማሌላንድ የባህር ዳርቻ ላይ የጦር ሰፈር በሊዝ ኪራይ እንደምታገኝ የተገለጸ ሲሆን፤ ሶማሌላንድ በበኩሏ፣ ለረዥም ጊዜያት ስትፈልገው የነበረውን እንደ አገር ዕውቅና የማግኘት ዕድል እንደሚፈጥርላት ባለሥልጣናቱ አመልክተዋል።
ለንግድ ስራ ሌላ ወደብ መገንባት ሳያስፈልግ፣ የበርበራ ወደብን ኢትዮጵያ እንደምትጠቀምበት የሶማሌላንድ ባለሥልጣናት  መግለጻቸው  የተዘገበ ሲሆን፤ ከዚህ ቀደም ኢትዮጵያ፣ ዲፒ ወርልድ እና ሶማሌላንድ የበርበራ ወደብን በጋራ  ለማልማት ስምምነት መፈጸማቸው ይታወሳል።

አበዳሪ ተቋም በማጣት ለረጅም ጊዜ የተንገላቱ ደንበኞችን የብድር አቅርቦት በአጭር ጊዜ በማስተካከል ትላንት ሚያዝያ 25 ቀን 2016 ዓ.ም መኪኖችን አስረክቧል::

ካፒታል የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኃላፊነቱ የተወሰነ የህብረት ስራ ማህበር ከግዙፉ የመኪና ገጣጣሚ አክሎክ ሞተርሰ ጋር ባለው ስምምነት መሰረት ከጠቅላላ 1 ሺ 20 መኪኖች ውስጥ በመጀመሪያው ዙር 20 መኪኖችን ለተበዳሪዎች አቅርበዋል::  በቀጣይም ለበርካታ አባላቶቹ ብድር ለማቅረብ ዝግጅቱን አጠናቋል::

በትላንትናው ዕለት በፖሊስ ተይዘው የተወሰዱ ሁለት የማሕበረ ቅዱሳን አመራሮች በዛሬው ዕለት ከእስር ተፈተው ወደ ቤታቸው መመለሳቸው ተሰምቷል፡፡ አመራሮቹ  በፖሊስ የተያዙትና የተወሰዱት  ከመኖሪያ ቤታቸው እንደነበር ታውቋል፡፡

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስትያን፣ ሰንበት ትምሕርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ (ማሕበረ ቅዱሳን) ሰብሳቢ የሆኑት ሊቀ ትጉሃን ቀሲስ ዶክተር ሙሉጌታ ስዩም እና የማሕበረ ቅዱሳን ዋና ጸሐፊ መምህር ዋሲሁን በላይ፣ ትላንት በፖሊስ ተይዘው ሜክሲኮ ወደሚገኘው የፌደራል ፖሊስ የወንጀል ምርመራ ቢሮ መወሰዳቸውን ማሕበረ ቅዱሳን ቴሌቪዥን ዘግቦ ነበርለ፡፡  

የሁለቱ አመራሮች መኖሪያ ቤት በትላንትናው ዕለት በፖሊስ የተፈተሸ ሲሆን፤ አመራሮቹ ተይዘው የተወሰዱበት ምክንያት እስካሁን  አልታወቀም፡፡

በተያያዘ ዜና፣ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስትያን ቅዱስ ሲኖዶስ ጽሕፈት ቤት ጸሐፊ ሆነው ሲያገለግሉ የነበሩት ሊቀ ማእምራን ብርሃኑ ተክለያሬድ ባለፈው ሳምንት  ሐሙስ ከመኖሪያ ቤታቸው በፖሊስ ተይዘው መወሰዳቸው ተነግሯል።

ባለቤታቸው ወይዘሮ ኢየሩሳሌም ተስፋው በፌስቡክ ገጻቸው ላይ ባጋሩት መረጃ፤ መሪጌታ ብርሃኑ በቁጥጥር ስር የዋሉት ከማለዳው 12 ሰዓት ላይ ነበር፡፡ ሊቀ ማእምራን “ለጥያቄ እንፈልግዎታለን” ተብለው ወደ ፌደራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ቢሮ እንደተወሰዱ ነው ባለቤታቸው ባጋሩት መረጃ  የጠቆሙት፡፡

ሊቀ ማእምራን ብርሃኑ፣ ከሳምንታት በፊት በቋሚ ሲኖዶስ ፈቃድ፣ የደቡብ አፍሪካ አሕጉረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ ተደርገው መዘዋወራቸው ታውቋል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለ2016 ዓ.ም የትንሣኤ በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ያስተላለፉት መልዕክት ሙሉ ቃል እንደሚከተለው ቀርቧል:-

እንኳን ለ2016 ዓ.ም የትንሣኤ በዓል በሰላም አደረሳችሁ!

ኢየሱስ ክርስቶስ መከራና ሞት፤ ግፍና ሙስናን፤ ሲዖልና መቃብርን አሸንፎ የተነሣበትን የትንሣኤ በዓል በየዓመቱ እናከብራለን። ከበዓሉ በፊት የሕማማትን ሰሞን እናሳልፋለን። ሰሞነ ሕማማቱ ፈተናን፣ ስቃይን፣ ክህደትን፣ አሳልፎ መስጠትን፣ የክፉዎችን ኅብረት፣ የምናስብበት ነው። ሐሰት ያሸነፈች፣ እውነት የተሸነፈች መስላ የታየችበት ነው። ብዙዎች መሥዋዕትነትን ፈርተው የሸሹበት ነው። አንዳንዶችን የሚያልፍ ጎርፍ ወሰዳቸው፤ አንዳንዶችን የሚሰክን ማዕበል ነጠቃቸው። ጥቂቶች ከሕማማቱ አልፈው ትንሣኤውን ለመመልከት ቻሉ።

የከተማው ጩኸት እና የሐሰቱ ወሬ እንኳን በሩቅ የነበሩትን፣ ቅርብ የነበሩትንም አሸንፏቸዋል። የሆሳዕና ዕለት ደግፈው የወጡት ከሦስት ቀን በኋላ ሊቃወሙ ሲወጡ ምንም አልመሰላቸውም። ድጋፋቸውም ተቃውሟቸውም ሁለቱም የጥቅም እንጂ የመርሕ አልነበረም። ሁለቱም ከእውነታው የተጣሉ ነበሩ። ሕማማት የውስጥና የውጭ ጠላቶች ተባብረውበታል። በሌላ ጊዜ ለሞት የሚፈላለጉ አካላት እውነትን ለመስቀል ሲሉ ግን ተባብረው ቆመዋል።

ሰዎቹ ያልተረዱት አንድ እውነታ ነበር። ከሕማማቱ ይልቅ ትንሣኤው ይበልጣል፤ ይረዝማልም። ሕማማቱ አምስት ቀን ሲሆን ትንሣኤው ግን አስር እጥፍ ይሆናል። የአምስት ቀን ፈተና የሃምሳ ቀን ዋጋ አለው። በርግጥ የሕማማቱን ሽብርና ዋይታ፣ መከራና እንግልት ለተመለከተ ትንሣኤ የሚመጣ አይመስለውም። ትንሣኤው ግን የታመነና የተረጋገጠ ነው። የበለጠ ማረጋገጥ የሚቻለውም ጸንቶ እንደ ዮሐንስ በመቆም ብቻ ነው።

ኢትዮጵያ በፈተና ውስጥ እያለፈች ነው። በፈተና ውስጥ የቆመች ሀገር ግን አይደለችም። በፈተና ውስጥ እያለፈች ያለች እንጂ። ወቅቱ ለኢትዮጵያ የሕማማት ሰሞን ይሆን ይሆናል። አራት ነገሮች ግን እውነት ናቸው። የመጀመሪያው የኢትዮጵያ ሕማማት አጭር መሆኑ፤ ሁለተኛው አጭር ቢሆንም ከባድ መሆኑ፤ ሦስተኛው ኢትዮጵያ ሕማማቱን ለማለፍ የሚያስችል ኃይል ያላት መሆኑ፤ አራተኛው ከአጭሩ ሕማማት በኋላ ረዥሙ የኢትዮጵያ ትንሣኤ የሚመጣ መሆኑ ነው።

የተነሣነው ኢትዮጵያ እንደምትፈተን ዐውቀንም፤ አምነንም ነው። ለዘመናት የኖሩ ስብራቶችንና ብልሽቶችን ልናክም ስንነሣ መንገዱ አልጋ በአልጋ አይሆንም። ከችግሩ ማትረፍ የለመዱ አካላት ዝም አይሉም፤ ኢትዮጵያ በማሽን እንደሚረዳ ሕመምተኛ ሆና በሞትና በሕይወት መካከል እንድትኖር የሚፈልጉ ኃይሎች ዐርፈው አይቀመጡም።

ግን ሕማማቱን እኛ ካልተቀበልንላት ለኢትዮጵያ ማን ይቀበልላታል የመከራውን ቀንበር ካልተሸከምንላት የሀገር ልጅነቱ የቱ ጋ ነው “ኢትዮጵያ ኢትዮጵያ” እያሉ በስሟ ሲምሉ የነበሩ ብዙዎች ነበሩ፤ ከልባቸው ለቃላቸው ታምነው ልጅ የሆኗት ግን ጥቂቶች ብቻ ናቸው። አንዳንዶች በስሟ የሚገዘቱት እንጀራዋን ለመብላት እንጂ መከራዋን ለመካፈል አይደለም፤ በተቃራኒው እንጀራዋን በልተው ተረከዛቸውን አነሡባት።

የሕማማቱ ወቅት አጭር ቢሆንም ከባድ መሆኑን እናውቃለን። የኮሶ መድኃኒት እንዲያሽር ከተፈለገ በአንድ ጊዜ በከባዱ መወሰድ አለበት። በትንሽ በትንሹ ከተወሰደ አያሽርም። የኢትዮጵያም ሕማማት እንደዚሁ ነው።

በፊስካል ፖሊሲ፣ በግብርና፣ በማኑፋክቸሪንግ፣ በውጭ ጉዳይ ፖሊሲ፣ በኅብረ ብሔራዊ አንድነት፣ ነጻነትን በማስተዳደር፣ በክልል አደረጃጀት፣ በሲቪል ሰርቪስ፣ በጋራ ትርክት ግንባታ፣ ወዘተ. የተረከብናቸው ውዝፍ ዕዳዎች ብዙ ናቸው። ወገባችንን አሥረን፣ እጅጌያችንን ሰብስበን መራራውን የኮሶ መድኃኒት ውጠን፣ እነዚህን ችግሮች ካልፈታናቸው ቆመው አይጠብቁንም። በፈጣኑ ዓለም ውስጥ ቀስ ብለን ልንሄድ አንችልም። ተጠንቅቀን ግን ፈጥነን፤ አስበን ግን ዋጋ ከፍለን መጓዝ አለብን። ይሄ ነው ሕማማቱን የሚያሳጥረው።

ኢትዮጵያ ሕማማቱን ለማለፍ የሚያስችል ኃይል አላት። ከዚህ በፊትም ብዙ አልፋለች፣ አሳልፋለች። የማይተዋት አምላክ አላት። የሚወዳት፣ የሚያስብላት ብቻ ሳይሆን የሚሞትላትም አመራር አላት። ዓላማ አይቶ ዋጋ የሚከፍል ሕዝብ አላት። አንጡራ ሀብት አላት። ይሄ የፈጣሪ፣ የአመራሩ፣ የሕዝቡ እና የአንጡራ ሀብቷ አራት ማዕዘናዊ ዐቅም፣ ሕማማቱን ማሳጠርና ማስቻል ብቻ ሳይሆን ቀጥሎ የሚመጣውን ፋሲካ ረዥም እንዲሆን ያደርገዋል።

ብርቱውን ይዘናል – እንበረታለን፤ ኃይል በሚሰጠው እንታመናለን። ንጽሕናንና ለሀገር ያለንን በጎ ራእይ መሠረት አድገን ቆርጠን እንሠራለን። የጥብርያዶስ ሞቅታም ሆነ የፕራይቶሪዮን ግቢ ጩኸት ከመንገዳችን አያቆሙንም።

የሆሳዕና ድጋፍም ሆነ የዕለተ ዓርብ ተቃውሞ መንገዳችንን አያስቀይሩንም። የኢትዮጵያን እውነት ብቻ ተከትለን እንገሠግሣለን። በዚህም ሕማማቱን አሳጥረን የኢትዮጵያን የትንሣኤ ጊዜ እናረዝመዋለን።

በድጋሜ መልካም የትንሣኤ በዓል!

ኢትዮጵያ በልጆቿ ጥረት ታፍራና ተከብራ ለዘላለም ትኑር!!

ፈጣሪ ኢትዮጵያና ሕዝቦቿን ይባርክ!

በአሁኑ ሰዓት በአሜሪካ እየተካሄደ በሚገኘው የዓለም ሮቦቲክስ ሻምፒዮን ላይ ኢትዮጵያውያን ተማሪዎች እየተሳተፉ እንደሚገኙ ለማወቅ ተችሏል።

ለዚህ የዓለም ሮቦቲክስ ሻምፒዮን ኢትዮጵያውያን ተማሪዎችን ይዘው ወደ አሜሪካ የተጓዙት የኢትዮ ሮቦ ሮቦቲክስ የትምህርትና ውድድር ማዕከል መሥራችና ዋና ሃላፊ አቶ ሰናይክሪም መኮንን ናቸው።

በአሜሪካው ውድድር ላይ ለመሳተፍ የተመረጡት ተማሪዎች በቅርቡ እዚህ አዲስ አበባ በኢሊሌ ሆቴል በተካሄደ የአፍሪካ ሮቦቲክስ ሻምፒዮና የላቀ ውጤት ያመጡ ሲሆን፤ በቪዛ መዘግየትና በቲክኒካል ጉዳዮች  ከጉዞው የቀሩም ተማሪዎች እንዳሉ ታውቋል።

NEW YORK (AP) — Officers took protesters into custody late Tuesday after Columbia University called in police to end the pro-Palestinian occupation on the New York campus.

The scene unfolded shortly after 9 p.m. as police, wearing helmets and carrying zip ties and riot shields, massed at the Ivy League university’s entrance. Officers breached Hamilton Hall, an administration building on campus, to clear out the structure.

The demonstrators had occupied Hamilton Hall more than 12 hours earlier, spreading their reach from an encampment elsewhere on the grounds that’s been there for nearly two weeks.

A statement released by a Columbia spokesperson late Tuesday said officers arrived on campus after the university requested help. The move came hours after NYPD brass said officers wouldn’t enter Columbia’s campus without the college administration’s request or an imminent emergency.

Hamilton Hall
“After the University learned overnight that Hamilton Hall had been occupied, vandalized, and blockaded, we were left with no choice,” the school’s statement said, adding that school public safety personnel were forced out of the building and one facilities worker was “threatened.”

“The decision to reach out to the NYPD was in response to the actions of the protesters, not the cause they are championing. We have made it clear that the life of campus cannot be endlessly interrupted by protesters who violate the rules and the law.”

Columbia’s protests earlier this month kicked off demonstrations that now span from California to Massachusetts. As May commencement ceremonies near, administrators face added pressure to clear protesters.

More than 1,000 protesters have been arrested over the last two weeks on campuses in states including Texas, Utah, Virginia, North Carolina, New Mexico, Connecticut, Louisiana, California and New Jersey, some after confrontations with police in riot gear.

In a letter to senior NYPD officials, Columbia President Minouche Shafik said it was making the request that police remove protesters from the occupied building and a nearby tent encampment “with the utmost regret.” She also asked that officers remain on campus through May 17, which is after the end of the university’s commencement celebrations.

“Walk away from this situation now and continue your advocacy through other means,” New York City Mayor Eric Adams advised the Columbia protesters on Tuesday afternoon before the police arrived. “This must end now.”

The White House earlier Tuesday condemned the standoffs at Columbia and California State Polytechnic University, Humboldt, where protesters had occupied two buildings until officers with batons intervened overnight and arrested 25 people. Officials estimated the northern California campus’ total damage to be upwards of $1 million.

  • ከ30ሺ በላይ ለሚሆኑ ጎብኚዎች ነጻ የህክምና ምርመራ ይሰጣል
            • ከህንድ፣ ዱባይ፣ ታይላንድ፣ ቱርክና ሌሎች አገራት የሚመጡ የጤና ተቋማትና ባለሙያዎች ይሳተፉበታል



       አፍሮ-ኤዥያ ዓለማቀፍ የጤና ኤክስፖ፣ እዚህ በመዲናዋ  ከግንቦት 9-11 ቀን 2016 ዓ.ም፣ በኤግዚቢሽን ማዕከል  እንደሚካሄድ አዘጋጆቹ ገለጹ፡፡ በኤክስፖው ላይ ከ400 በላይ የአገር ውስጥና የውጭ ድርጅቶች፣ ከ30ሺ በላይ ጎብኚዎችና  ከ2ሺ በላይ የጤና አጠባበቅ ባለሙያዎች ይሳተፉበታል ተብሏል፡፡
የጤና ኤክስፖውን አስመልክቶ አዘጋጆቹና አጋር ተቋማት፣ ባለፈው ሰኞ ሚያዝያ 14 ቀን 2016 ዓ.ም በራማዳ  ሆቴል የሚዲያ ባለሙያዎችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት  ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል፡፡
በጋዜጣዊ መግለጫው ላይ እንደተመለከተው፣ በጤና ኤክስፖው  ላይ የፓናል ውይይቶች፣ ዎርክሾፖችና ኤግዚቢሽኖችን ጨምሮ በርካታ ኹነቶች ይቀርባሉ፡፡ የጤና ባለሙያዎች የልምድ ልውውጥ የሚያደርጉበትና የቴክኖሎጂና የዕውቀት ሽግግር የሚካሄድበት እንዲሁም የትስስርና ትብብር ዕድሎች የሚፈጠርበት  መድረክም እንደሚሆን ተጠቁሟል፡፡
 “ድልድዮችን እንገንባ፣ ህይወትን እናድን” በሚል መሪ ቃል በሚካሄደው በዚህ ዓለማቀፍ ኤክስፖ፤ ከ30ሺ በላይ ለሚሆኑ ጎብኚዎች ነጻ የጤና ምርመራ እንደሚከናወን የተገለጸ ሲሆን፤ ለጤና  ባለሙያዎችም ነጻ ሥልጠና እንደሚሰጥ ለማወቅ ተችሏል፡፡  
ለሦስት ቀናት በሚቆየው የአፍሮ- ኤዥያ ዓለማቀፍ የጤና ኤክስፖ ላይ ከህንድ፣ ዱባይ፣ ታይላንድ፣ ቱርክ፣ ኢንዶኔዥያ፣ ማላይዥያና ሌሎችም አገራት የተውጣጡ በጤና ላይ የሚሰሩ ተቋማትና ባለሙያዎች እንደሚሳተፉበት ተጠቁሟል፡፡  ኤክስፖው ከወትሮው በተለየ በቢዝነስ ላይ ብቻ የሚያተኩር ሳይሆን፣ ተቋማት ማህበራዊ ሃላፊነታቸውን ለመወጣት ልዩ ዕድል የሚያገኙበት እንደሆነም ተነግሯል፡፡
ይህን ዓለማቀፍ የጤና ኤክስፖ ኤፍዚ ማርኬቲንግና ኮምዩኒኬሽን ኃ.የተ.የግ. ማህበር ከሰላም ኸልዝ ኮንሰልታንሲ ጋር በመተባበር ያዘጋጀው ሲሆን፤ ሳልማር ኮንሰልታንሲ፣ የኢትዮጵያ ጤና ሚኒስቴር፣ የኢፌዲሪ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ባለሥልጣን፣ የኢትዮጵያ ምግብና መድሃኒት ባለሥልጣን፣ የአዲስ አበባ ጤና ቢሮ፣ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የምግብና መድሃኒት ባለሥልጣን እንዲሁም የአዲስ አበባ ንግድና ዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት በአጋርነት እንደሚሳተፉበት ታውቋል፡፡

 መንግሥት ለእንዲህ ያሉ ተቋማት ድጋፍ እንዲያደርግ ተጠየቀ



          ከተከፈተ 17ኛ ዓመቱን ያስቆጠረውና እስካሁን ከ3ሺ800 በላይ የፋሽን ዲዛይነሮችን አሰልጥኖ ያስመረቀው ኔክስት ፋሽን ዲዛይን ኮሌጅ ፤ አዲሱን ከፍተኛ የማስተር ክላስ ሥልጠናውን ባለፈው ቅዳሜ ምሽት ሚያዝያ 12 ቀን 2016 ዓ.ም ቦሌ ዩጎ ሰርች አጠገብ በሚገኘው ሪያሊቲ ፕላዛ ህንጻ ላይ በይፋ መጀመሩን አስታወቀ፡፡
የፋሽን ማስተር ክላስ ለተማሪዎቹ ከሚሰጣቸው ሥልጠናዎች መካከል፡- ስፔሻል ፓተርን ዲዛይን፣ አርት ድሮዊንግ፣ ፋብሪክ ፔይንቲንግ፣ ፋሽን ስታይሊንግ፣ 3ዲ ዲዛይን፣ ፋሽን ማኔጅመንትና ሌሎችም ይገኙበታል ተብሏል፡፡
የኔክስት ፋሽን ዲዛይን ኮሌጅ መሥራችና ባለቤት ወ/ሮ ሣራ መሃመድ በምሽቱ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ፤ “ማስተሪንግ ክላስ ሰዎች እንደ መክሊታቸው (ተሰጥኦዋቸው) ከፍተኛና ልዩ ሥልጠና የሚያገኙበት ፕሮግራም ነው” ብለዋል፡፡
በምሽቱ በኔክስት ፋሽን ዲዛይን ኮሌጅ ተመራቂዎች የተዘጋጀ አስደማሚ የፋሽን ትርኢት ለታዳሚዎች የቀረበ ሲሆን፤ ሞዴሎች የተለያዩ የፋሽን ዲዛይን ውጤቶችን ያሳዩት በመድረክ ላይ በቄንጥ እየተራመዱ ሳይሆን በየቦታው እንደ ሃውልት ወይም የቅርስ ጥበብ በየቦታው ተገትረው ነበር - በመጀመሪያ እይታ በልብስ መሸጫ መደብሮች የሚታዩትን አሻንጉሊቶች የመሰሏቸውም አልጠፉም፡፡
ኮሌጁ ባለፉት ዓመታት ከዓለማቀፍ ተመሳሳይ የማሰልጠኛ ተቋማት ጋር በፈጠረው መልካም የሥራ ግንኙነት 42 ዲዛይነሮች በህንድ አገር ሙሉ የነጻ ትምህርት እንዲያገኙ ያደረገ ሲሆን፤ሥልጠናቸውን ተከታትለው በመመለስም ለኢንዱስትሪውና ለአገራቸው ትልቅ አስተዋጽኦ እያበረከቱ እንደሆነ ለማወቅ ተችሏል፡፡ ኮሌጁ ከሥልጠናው ጎን ለጎን፣ የተለያዩ የፋሽን ትርኢቶችን ከአገር ውስጥ ባሻገር በኒውዮርክ፣ ፈረንሳይ፣ ጣልያን፣ ጀርመን፣ ስዊዘርላንድ፣ ኡጋንዳና ሌሎችም አገራት በማቅረብ ስኬትና ዕውቅና ተቀዳጅቷል ተብሏል፡፡
ኔክስት ፋሽን ዲዛይን ኮሌጅ፤ በቅርቡ ከሳውዲ አረቢያ ተባረው ወደ አገራቸው የተመለሱ እንስት ኢትዮጵያውያንን በነጻ በማሰልጠን የሥራ ዕድል እንዲያገኙና ለሌሎች የሥራ ዕድል እንዲፈጥሩ ማስቻሉ ይነገርለታል፡፡ ሴቶችን ፋሽን ዲዛይንና ሞዴሊንግን ጨምሮ በሌሎች ዘርፎች በማሰልጠን ጉልህ አስተዋጽኦና ተጽዕኖ በመፍጠር ላይ የሚገኘው ኮሌጁ፤ እስካሁን የራሱን መሬት ባለማግኘቱ ለህንጻ ኪራይ ከፍተኛ ወጪ እንደሚያወጣ የተናገሩ አንድ የዕለቱ የክብር እንግዳ፤መንግሥት ለእንዲህ ዓይነቶቹ  ተቋማት ትኩረት ሰጥቶ መደገፍ እንዳለበት አሳስበዋል፡፡ “እኔ መንግሥት ብሆን መሬት የምሰጠው እንደ ኔክስት ፋሽን ኮሌጅ ላሉ የግል ተቋማት ነው፡፡” ሲሉም አክለዋል፡፡

 ዘመን ባንክ፤ የሠራተኞቹን ዕውቀትና ክህሎት ለማሳደግ፣ በዓለም  ትልቁ የኢንተርኔት የመማሪያ መድረክ ከሆነው ሊንክድኢን ለርኒንግ ጋር የአጋርነት ስምምነት ተፈራረመ፡፡
የዘመን ባንክ የሰው ሀብት ምክትል ዋና ኦፊሰር አቶ ታከለ ዲበኩሉ ስምምነቱን አስመልክቶ ባደረጉት ንግግር፤ “ዘመን ባንክ ለሰራተኞቹ ቀጣይነት ያለው የመማርና የሙያ እድገት ባህልን ለማሳደግ ቁርጠኛ ነው። ከሊንክድኢን ለርኒንግ ጋር ያደረግነው ስምምነት፣ ይህንን ቁርጠኝነት የሚያጎላ ከመሆኑም ባሻገር ሠራተኞቻችን የፋይናንስ ዘርፉ  የሚጠይቀውን ችሎታ፣ እውቀትና ክህሎት እንዲያዳብሩ  የሚረዳ ነው፡፡” ብለዋል፡፡
የሊንክድኢን ታለንት ሶሉዩሽን ዋና ኃላፊ ማቲው ግሬይ በበኩላቸው፤ ”ከዘመን ባንክ ጋር ያደረግነው ስምምነት የሰራተኞቹን የክህሎትና የእውቀት ክፍተቶች ለማሟላት እድሉን የሚሰጠን ከመሆኑም በላይ ሊንክድኢን ለርኒንግ በአፍሪካ ተመራጭ የክህሎት ልማት መድረክ ሆኖ  መቀጠሉን ስለሚያሳይ እጅግ ተደስተናል።“ ብለዋል፡፡
ኃላፊው አክለውም፤“ የዘመን ባንክ የሰው ሃብት ስትራቴጂ በቀጣይ አመታት ይበልጥ እንዲጎለብትና ውጤታማ እንዲሆን አብረን እንሰራለን።” ሲሉ ተናግረዋል፡፡



       ”--ካሙ የሳትረ የቅርብ ወዳጅ ነበር፡፡ ሆኖም ወዳጅነታቸዉ ከዘጠኝ አመት በኋላ በ1952 ዓ.ም ተቋጭቷል፡፡ በሁለቱ መካከል መቃቃር እንዲፈጠር ያደረገዉ ዐቢይ ምክንያት ካሙ በኮሚኒዝም ላይ ያንፀባርቀዉ የነበረዉ ትቸት ነዉ፡፡ አንድሬ ዢድ፣ ሊዮ ቶልስቶይ፣ ፊዮዶር ዶስቶቭስኪ፣ ሄርማን መልቬል እና ፍራንዝ ካፍካ ካሙ ላይ ታላቅ ተፅዕኖ የፈጠሩ ስመ ጥር ልብ ወለድ ደራሲያን ናቸዉ፡፡ --”
               መኮንን ደፍሮ


       (ክፍል አንድ)
ሕይወት እና ሥራዎች
አልበርት ካሙ ፈረንሳዊ ፈላስፋ፣ ልብ ወለድ ጸሐፊ፣ ጸሐፌ ተዉኔት፣ የቴአትር ተዋናይ፣ ጋዜጠኛ እና የፖለቲካ አክቲቪስት ነበር፡፡ ካሙ ጥቅምት 7 ቀን 1913 ዓ.ም ሞንዶቪ ዉስጥ ከገበሬ ወላጆቹ ተወለደ፡፡ ሞንዶቪ ቦን በተባለ የፈረንሳይ ቅኝ ግዛት ውስጥ የምትገኝ ትንሽ የምስራቅ አልጀሪያ ከተማ ናት፡፡
ካሙ ገና ጨቅላ ሳለ ነበር በአንደኛዉ የዓለም ጦርነት አባቱን ሉሲያ ኦጉስት ካሙን በሞት ያጣዉ፡፡ በእዚህም ምክንያት የአደገዉ የእስፔን የዘር ሐረግ ባላት እናቱ ካትሪን ሄለን ስንቴስ እጅ ነዉ፡፡ ስንቴስ ስሟን እንኳ መጻፍ የማትችል መሀይም ነበረች፡፡ ካሙ የልጅነት ጊዜዉን ያሳለፈዉ በአስከፊ ድህነት ዉስጥ ነበር፡፡ በ1932 ዓ.ም አልጀርስ ዩኒቨርሲቲ ገብቶ ፍልስፍና አጥንቷል፡፡ በ1942 ዓ.ም በገጠመዉ የሳንባ ደዌና አልጀሪያ ዉስጥ በነበረዉ የፖለቲካ ጭቆና ምክንያት አልጀሪያን ለቆ ወደ እናት አገሩ ፈረንሳይ አቀና፡፡ ፈረንሳይ ከገባ በኋላ በ1943 ዓ.ም ኮምባት ተብሎ የሚጠራዉንና ፈረንሳዮች የጀርመን ናዚን ወረራ በመቃወም ንቅናቄ ያደርጉበት የነበረዉ ምስጢራዊ ጋዜጣ ዋና አዘጋጅ ሆኖ ሥራ ጀመረ፡፡ ከእዚህ ጋዜጣ ተሳታፊ ጸሐፍት አንዱ ዠን-ፖል ሳትረ ነበር፡፡
ጁሊያን ያንግ የተባለ የፍልስፍና ምሁር እንደ ገለፀዉ፣ ካሙ መልኩ አሜሪካዊዉን የፊልም ተዋናይ ሃምፕሬይ ቦጋርትን የሚመስል፣ ብዙ ጊዜ ከአፉ ጥግ ሲጋራ የማይጠፋ መልከ መልካም ነበር፡፡ ዘ አፍሪካን ኩዊን በተሰኘዉ የፊልም ሥራዉ ባሳየዉ ድንቅ ትወናዉ፣ በ1952 ዓ.ም ታላቁን የፊልም ሽልማት ኦስካር ያሸነፈዉ ሃምፕሬይ ቦጋርት፤በሲኒማ ታሪክ ስማቸዉ ጎልቶ ከሚጠቀስ ኮከቦች መካከል አንዱ ነዉ፡፡ ካሙ ሸበላነቱም ከሴቶች ጋር በቀላሉ እንዲቀራረብ አግዞታል፡፡ ይህ መልከ መልካም ሰው ለትዳር አጋሮቹ የማይታመን ሴት አውል ነበር፡፡ ካሙ ገና በወጣትነት ዕድሜዉ ጎጆ የቀለሰ ሰው ነበር፡፡ በ1934 ዓ.ም የአስራ ዘጠኝ አመት ወጣት ሳለ የመጀመሪያ የትዳር አጋሩን ሲሞን ሃይን አገባ፡፡ ሆኖም በሚስቱ አመንዝራነት ምክንያት ከአንድ አመት በኋላ ትዳራቸዉ በፍቺ ተቋጭቷል፡፡ ቆይቶ በ1940 ዓ.ም በሃያ ስድስ ዓመቱ ሁለተኛ ሚስቱን ፒያኒስትና የሒሳብ ሊቋን ፍራንሲን ፋዉርን አገባ፡፡ ከእሷ ሁለት መንታ ልጆችን አፍርቷል፡፡    
ካሙ ወደ ሥነጽሑፉ ዓለም እንዲቀላቀል በጎ ተፅእኖዉን ያሳረፈበት የፍልስፍና መምህሩ ዠን ግረነር ነዉ፡፡ ካሙ በሕግ የሚፈፀምን የሞት ቅጣ በፅኑ በማዉገዝ የሚታወቅ ፈላስፋ ነበር፡፡  ካሙ በመጀመሪያ ደረጃ ራሱን ጸሐፊ እንጂ ፈላስፋ አድርጎ አይቆጥርም ነበር፡፡ ይህ ሰው ሥራዎቻቸዉ በዓለም ዙሪያ በስፋት ከተነበቡላቸዉ ዘመናዊ ፈረንሳዊያን ደራሲያን መካከል አንዱ ነዉ፡፡   
ካሙ የሳትረ የቅርብ ወዳጅ ነበር፡፡ ሆኖም ወዳጅነታቸዉ ከዘጠኝ አመት በኋላ በ1952 ዓ.ም ተቋጭቷል፡፡ በሁለቱ መካከል መቃቃር እንዲፈጠር ያደረገዉ ዐቢይ ምክንያት ካሙ በኮሚኒዝም ላይ ያንፀባርቀዉ የነበረዉ ትቸት ነዉ፡፡ አንድሬ ዢድ፣ ሊዮ ቶልስቶይ፣ ፊዮዶር ዶስቶቭስኪ፣ ሄርማን መልቬል እና ፍራንዝ ካፍካ ካሙ ላይ ታላቅ ተፅዕኖ የፈጠሩ ስመ ጥር ልብ ወለድ ደራሲያን ናቸዉ፡፡
ካሙ፣ ገና በጎልማሳነት እድሜዉ በመኪና አደጋ ቢቀጭም፣ እጅግ ታላላቅ የሥነጽሑፍና የፍልስፍና ሥራዎችን ለዓለም አበርክቷል፡፡ ካሙ በ1937 ዓ.ም ያሳተመዉ የወግ ሥራዉ ቢቲዊክስ ኤንድ ቢቲዊን ይሰኛል፡፡ በቀጣዩ ዓመት በ1938 ዓ.ም ያሳተመዉ ሥራዉም ወግ ሲሆን፤ ነፕሾልስ ይሰኛል፡፡ በ1942 ዓ.ም ዘ ስትሬንጀር የተሰኘ የልብ ወለድ ሥራዉን አሳትሟል፡፡ ይህ ሥራ ለህትመት በበቃበት ወቅት ሳትረ ሳይቀር ታላቅ የፈጠራ ሥራ መሆኑን አወድሶ ኂሳዊ መጣጥፍ ጽፏል፡፡ ዘ ስትሬንጀር በብዛት የተሸጠና ከአርባ በላይ ወደ ሆኑ ቋንቋዎች የተተረጎመ የሃያኛዉ ክፍለ ዘመን የፈረንሳይ ልብ ወለድ ነዉ፡፡ የእዚህ ሥራ ዐቢይ ሴማ ወለፈንድ ነዉ፡፡ በእዚሁ አመት ያሳተመዉ ታላቅ የፍልስፍና ሥራዉ ዘ ሚዝ ኦፍ ሲስፈስ ኤንድ አዘር ኢሴይስ ይሰኛል፡፡ ይህ ሥራው ዘ ስትሬንጀር ዉስጥ የዳሰሰዉን ወለፈንድ በጥልቀት የፈከረበት ሥራዉ ነዉ፡፡ በ1944 ዓ.ም ለመድረክ የበቃ የተዉኔት ሥራዉ ክሮስ ፐርፐዝ ይሰኛል፡፡ ካሊጉላ በቀጣዩ ዓመት በ1945 ዓ.ም ለመድረክ የበቃ የተዉኔት ሥራዉ ነዉ፡፡ እነዚህን ሥራዎች ተከትሎ በ1948 ዓ.ም ስቴት ኦፍ ሲይጂ፣ በ1950 ዓ.ም ደግሞ ዘ ጄስት የተሰኙት ሥራዎቹ ለመድረክ በቅተዋል፡፡ በ1947 ዓ.ም ያሳተመዉ ዝነኛ የልብወለድ ሥራዉ ዘ ፕለይግ ይሰኛል፡፡ በ1951 ዓ.ም ዘ ሪቤል፣ አን ኢሴይ ኦን ማን ኢን ሪቮልት የተሰኘዉን ሥራዉን አሳተመ፡፡ በ1956 ዓ.ም ያሳተመዉ ሌላኛዉ የልብ ወለድ ሥራዉ ዘ ፎል ይሰኛል፡፡ ከአንድ አመት በኋላ በ1957 ዓ.ም ኤግዛይል ኤንድ ዘ ኪንግደም የተሰኘ ሥራዉን አሳትሟል፡፡ ካሙ ከሞተ በኋላ በ1994 ዓ.ም በሕይወት ሳለ ጽፎ ያላገባደደዉ የሕይወት ታሪኩ ላይ የተመሠረተዉ የልብ ወለድ ሥራዉ ዘ ፈርስት ማን ታተመ፡፡ ይህ ሥራ ካሙ ላይ የመኪና አደጋ በደረሰበት ወቅት ሳምሶናይቱ ዉስጥ የተገኘ ሥራ ነዉ፡፡ ከእዚህ ድርሰቱ ጋር አብሮ የተገኘው ሌላኛው መጽሐፍ የፍሪድሪክ ኒቼ ዘ ጌይ ሳይንስ ነው፡፡                
ካሙ ለዓለም ሥነጽሑፍ ማለፊያ ሥራዎችን በማበርከቱ  October 16 1957 ዓ.ም ታላቁን የኖቤል ሽልማት በሥነጽሑፍ ተሸልሟል፡፡ ነገር ግን የኖቤል ሽልማትን ከተቀበለ በኋላ በእዚህ ዓለም የኖረዉ ለሦስት ዓመታት ብቻ ነዉ፡፡ ካሙ በተወለደ በአርባ ስድስት አመቱ የጋሊማርድ አሳታሚ ባለቤት ጋስቶኦን ጋሊማርድ ዘመድ ከሆነዉ ጓደኛዉ ሚሼል ጋሊማርድ ጋር ከመኖሪያ መንደሩ ሎርምረን ወደ ፓሪስ በመኪና እየተመለሱ ሳለ፣ በመኪና አደጋ ጥር 4 ቀን 1960 ዓ.ም ከእዚህ ዓለም በሞት ተለየ፡፡ ካሙ እና ሚሼል ጋሊማርድ መኪና በፍጥነት የማሽከርከር ሱስ ነበረባቸዉ፡፡ የካሙ ሥርዓተ ቀብር የተፈፀመው ሎርምረን ውስጥ ነው፡፡  
፩. የሕይወት ትርጉም
የበርካታ ፈላስፎችን ትኩረት ከሳቡ ዐቢይ ፍልስፍናዊ ጉዳዮች መካከል አንዱ የሕይወት ትርጉም ነዉ፡፡ ለእዚህ ወሳኝ ፍልስፍናዊ ጉዳይ ልዩ ትኩረት ሰጥተዉ ከተፈላሰፉ ፈላስፎች መካከል አንዱ ካሙ ነዉ፡፡ ካሙ ዘ ሚዝ ኦፍ ሲስፈስ በተሰኘ የፍልስፍና ሥራው እንደሚነግረን፣ ሕይወት ፋይዳ አለዉ ወይስ የለዉም የሚለዉ ጥያቄ ፍልስፍና ሊመልሰዉ የሚገባ እጅግ አንገብጋቢ ጥያቄ ነዉ (ካሙ፣ 1955)፡፡ ለካሙ ከሕይወት ትርጉም ጥያቄ የሚቀድም ወሳኝ ጥያቄ የለም፡፡ ለእሱ የሕይወት ትርጉም ፍልስፍና ሊፈታው የሚገባ ብቸኛው ወሳኝ ተግዳሮት የሆነው ራስን ከማጥፋት ድርጊት ጋር በቀጥታ ስለሚሰናሰል ነው፡፡
ወለፈንድ         
ዘ ሚዝ ኦፍ ሲስፈስ ካሙ የሕይወት ወለፈንድነት ወይም ትርጉም አልባነት ምንጩ ምን እንደ ሆነ እንዲሁም ሕይወት ፋይዳ ቢስ በመሆኑ ምክንያት ራስን መግደል ተገቢ ነዉ አይደለም የሚለዉን ጥያቄ የመለሰበት ፍልስፍናዊ ሥራዉ ነዉ፡፡ ብዙ ጊዜ ግለሰቦች ራሳቸዉን ለመግደል ዉሳኔ ላይ የሚደርሱት የሕይወትን ወለፈንድነት ወይም ከንቱነት ሲረዱ ነዉ (ዊክ፣ 2003)፡፡ ለካሙ ሕይወት ወለፈንድ ነው (ቶዲ፣ 1959)፡፡ ይህ ሐቅ የሰዉ ልጅ ፈፅሞ ሊሸሸዉ የማይችለዉ ሐቅ ነዉ፡፡
እንደ ካሙ እሳቤ፣ የሕይወት ወለፈንድነት ምንጩ በፍፁማዊ ትርጉም ፈላጊዉ የሰዉ ልጅና በፍፁማዊ ትርጉም አልባዉ ሁለንታ መካከል ያለ ግጭት፣ ሞት አይቀሬ ታላላቅ ስኬቶቻችንን ሁሉ በቅፅበት መና አንደሚያደርጋቸዉ መታዘባችን፣ ሁለንታ ለእኛ ትልምና ፍላጎት መልስ አልባ መሆኑን መታዘባችን፣ የሰዉ ልጅ ኅሊና የሁለንታን ምስጢር ለመግለፅ ብቁ አለመሆኑ እና የዉሃ ቅዳ ዉሃ መልስ ጨዋታ የሆነዉን አታካቹን የሰርክ ሕይወታችንን መታዘብ ነዉ (ካሙ፣ 1955፤ ቶዲ 1959፤ ኮፕልስተን፣ 1994፤ ደ ሉፕ፣ 1966፤ ዌበር 2018፤ ቤኔት 2001፤ ፎለይ 2008፤ ኮፕልስተን፣ 1956)፡፡ ዮንግ (2003) እንደሚነግረን፣ ለካሙ የሰው ልጅ ሕልውና ትርጉም አልባ የሆነበት ሰበብ፣ የፈጣሪ በህልውና አለመኖር ነው  (ዮንግ፣ 2003)፡፡  
ራስን ማጥፋት      
ካሙ እንደሚነግረን፣ ሰዉ ከሕይወት ከንቱነት ሐቅ ጋር ሲላተም ራስን ማጥፋትን መፍትሄ አድርጎ ይወስዳል (ዮንግ፣ 2003)፡፡ ራስን የመግደል ስሜት ሬስቶራንትን ጨምሮ በማንኛውም ጊዜ ሊፈጠር ይችላል (ካሙ፣ 1955)፡፡ ለመሆኑ ራስን መግደል የሕይወት ፋይዳ ቢስነት ትክክለኛ መፍትሄ ይሆናል? በፍፁም ይለናል ካሙ፡፡ እንደ እሱ እሳቤ፣ ራስን መግደል የሕይወት ፋይዳ ቢስነት ስሜት ትክክለኛ መድኃኒት አይደለም፡፡ በመሆኑም ተግባሩ በፅኑ የሚወገዝ ነው፡፡    
ተስፋ
ለካሙ እንደ ራስን መግደል ሁሉ ተስፋ፣ ቂል ሰው ለወለፈንድ ስሜት ትክክለኛ መፍትሄ አድርጎ የሚወስደው፣ በእውነቱ ግን ትክክል ያልሆነ መፍትሄ ነው (ዊክ፣ 2003)፡፡ ተስፋ ካሙ አበክሮ የሚተቸው የዴንማርካዊዉን ኤግዚስቴንሻሊስት ፈላስፋ ሶረን ኪርክጋርድ ጽንሰ ዐሳብ ነው፡፡ ይህ ጽንሰ ዐሳብ ከሃይማኖታዊ እሳቤ ጋር የተሰናሰለ ሲሆን፤ወለፈንድን ከመጋፈጥ ይልቅ በሰማያዊ ሕይወት ተስፋ ማድረግንና ከፈጣሪ ጋር ህብረት መፍጠርን ይሰብካል፡፡ እንደ ካሙ እሳቤ፣ ተስፋ ለሕይወት ፋይዳ ቢስነት ተግዳሮት ትክክለኛ መፍትሄ ሆኖ መቅረብ አይችልም፡፡ ተስፋ ለካሙ ወለፈንድን የመሸሽ ተግባር በመሆኑ የተወገዘ ነዉ (ዊክ፣ 2003)፡፡ የካሙ ፍልስፍና የሚነግረን፣ በእዚህ ዓለም እየኖርነው ካለነው ሕይወት ውጪ ሌላ ተስፋ የምናደርገው ሕይወት አለመኖሩን ነው፡፡ ለካሙ፣ ተስፋ ፍልስፍናዊ ራስን ማጥፋት ነው፡፡ ለምን ቢባል ምክንያታዊነትን መግደል ስለሆነ (ዮንግ፣ 2003)፡፡
ከላይ እንዳየነው ለካሙ ራስን ማጥፋትም ሆነ ተስፋ ለወለፈንድነት ስሜት ትክክለኛ መፍትሄዎች አይደሉም፡፡ ታዲያ እውነተኛ መፍትሄው ምንድር ነው? ካሙ እንደሚነግረን፣ የወለፈንድነት ስሜት ትክክለኛው መፍትሄ አድማ ነው፡፡ ይህን ጽንሰ ዐሳብ በቀጣዩ ጽሑፍ እናያለን፡፡            
ከአዘጋጁ፡-
መኮንን ደፍሮ ልብወለድ ጸሐፊ፣ ገጣሚ እና የሥነ ጽሑፍ ኀያሲ ነው፡፡ የባችለር ድግሪውን በ2009 ዓ.ም፣ የማስተርስ ድግሪዉን ደግሞ በ2015 ዓ.ም ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በፍልስፍና አግኝቷል፡፡ በተማረው የሙያ መስክ በጅማ፣ በመቐለ እና በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በመምህርነት ሠርቷል፡፡ ጸሐፊው አዲስ አድማስ ጋዜጣን ጨምሮ በተለያዩ መጽሔቶች ግጥሞቹንና የልብ ወለድ ሥራዎቹን አሳትሟል፡፡      መኮንን በርካታ የኢትዮጵያ ታላላቅ ደራሲያን ሥራዎች ላይ ኂሳዊ መጣጥፎችን ጽፏል፡፡

Page 2 of 705