Administrator

Administrator

የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ ቢሊየነር ኻላፍ አህመድ አል ሀብቱር፣ በዓለም ዋንጫው ላይ አስደናቂ ተሳትፎ ላደረገው የግብፅ ብሔራዊ ቡድን ልዑካን በሙሉ አዳዲስ የ ሚትሱቢሺ መኪኖችን በስጦታ አበረከተ።
ይህ እጅግ ውድ የሆነው ስጦታ ተጫዋቾችን፣ አሰልጣኞችን፣ የህክምና ባለሙያዎችንና ለቡድኑ ስኬት አስተዋፅኦ ያደረጉ አስተዳዳሪዎችን በሙሉ ያካተተ ነው። ቢሊየነሩ አል ሀብቱር ስጦታውን ያበረከተው ለመላው የአረብ ዓለም ኩራት ለሆነው የግብፅ ቡድን ያለውን ክብር ለመግለፅ እንደሆነ ተናግሯል።
Great Africa-
* ሞሮኮ - 31.5 ሚሊዮን ዶላር
የአፍሪካ ሀገራት በ2026 የፊፋ የዓለም ዋንጫ ላይ ካሳዩት አስደናቂ ተሳትፎ ጎን ለጎን እጅግ ከፍተኛ የገንዘብ ሽልማት ይዘው ወጥተዋል። አስደናቂ ጉዞ ያደረገችው ሞሮኮ 31.5 ሚሊዮን ዶላር በመሰብሰብ ከአፍሪካ ቀዳሚዋ ሀገር መሆን ችላለች።
ግብፅ በበኩሏ 17.5 ሚሊዮን ዶላር በማግኘት ሁለተኛ ደረጃን ስትይዝ፤ ሴኔጋል፣ አልጄሪያ፣ ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ፣ ኬፕ ቨርዴ፣ ኮትዲቩዋር፣ ደቡብ አፍሪካ እና ጋና እያንዳንዳቸው 13.5 ሚሊዮን ዶላር አግኝተዋል። ቱኒዝያ ደግሞ 10.5 ሚሊዮን ዶላር ማግኘት ችላለች።
G.A-
የብፁዕ ካርዲናል አቡነ ብርሃነኢየሱስ እና የብፁዕ አቡነ ጸጋዬ 50ኛ ዓመት የወርቅ ኢዮቤልዩ የክህነት አገልግሎት ክብረ በዓል በልደተ ማርያም ካቶሊክ ካቴድራል በመስዋዕተ ቅዳሴ በድምቀት ተከብሯል።
በዕለቱ የርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንሲስ (በቅድስት መንበር ተወካይ ብፁዕ ሊቀጳጳስ ብሪያን አማካይነት የቀረበ) የመልካም ምኞት መልዕክት የተላለፈ ሲሆን፥ ቅዱስነታቸው ብፁዓን ጳጳሳቱ ለሰዉ ልጅ ሁለንተናዊ ክብርና ለኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ላበረከቱት ከግማሽ ክፍለ ዘመን በላይ የሆነ የፅናት አገልግሎትና ከፍተኛ አሻራ ምስጋና አቅርበዋል።
ለብዙዎች አብነት የሆኑት እነዚህ አባቶች በተለይም በኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን የጳጳሳት ጉባኤ ጠቅላይ ጽ/ቤት እድገት ውስጥ የላቀ አስተዋፅዖ አበርክተዋል። ብፁዕ ካርዲናል አቡነ ብርሃነኢየሱስ በጠቅላይ ጽ/ቤት ፕሬዝደንትነት ከ26 ዓመታት በላይ በመምራት፣ ብፁዕ አቡነ ጸጋዬ ደግሞ ተቋሙን በአሁናዊ መዋቅሩ በማደራጀት ለ9 ዓመታት በጠቅላይ ጸኃፊነት በቁርጠኝነት በማገልገል የቤተክርስቲያኒቱ የዕድገት ምሰሶ መሆናቸው በበዓሉ ላይ ተገልጿል።
በዓለማችን አዳዲስ የቤት ግንባታ ቋንቋዎች የሆኑት የ3ዲ ኮንክሪት ሕትመት (3D Printing)፣ ቀላል የዓረብ ብረት ግንባታ እና የኮንቴይነር መኖሪያ ቤት ቴክኖሎጂዎች በኢትዮጵያ በስፋት ሥራ ላይ መዋል ጀምረዋል።
በአዲስ አበባና በተለያዩ ከተሞች ያለውን ከፍተኛ የቤት አቅርቦት እጥረት፣ የቤት ኪራይ ንረት እና የኑሮ ውድነት በአፋጣኝ ለመቅረፍ መንግሥት እነዚህን ሦስት ዘመናዊና ወጪ ቆጣቢ ዘዴዎች በማጣመር አዲስ ተስፋ ይዞ ብቅ ብሏል። በ10 ዓመቱ መሪ የልማት ዕቅድ 4.4 ሚሊዮን ቤቶችን ለመገንባት የታለመ ሲሆን፥ ይህንን ለማሳካትም የግል አልሚዎች በስፋት እንዲሳተፉ እና ዜጎች በማኅበር ተደራጅተው የመሬት አቅርቦት እንዲያገኙ እየተደረገ ይገኛል።
ከእነዚህ ቴክኖሎጂዎች መካከል የ3ዲ ሕትመት ልዩ ትልቅ ፕሪንተር በመጠቀም ግንባታን የሚያከናውን ሲሆን፥ የብረት ግብዓትን እስከ 30 በመቶ፣ ሲሚንቶን ደግሞ ከ35 እስከ 40 በመቶ በመቀነስ ወጪን በከፍተኛ ደረጃ ይቆጥባል። በአሁኑ ወቅት ባለ 4 ወለል (G+4) ቤቶች በዚህ ዘዴ እየተገነቡ ሲሆን፣ ዲዛይኑ እስከ 14 ወለልና ከዚያ በላይ የመገንባት አቅም አለው። በተጨማሪም ቀላል የዓረብ ብረት ግንባታ ክፍሎች በፋብሪካ ተዘጋጅተው በቦታው ላይ የሚገጣጠሙ በመሆናቸው፣ ፈጣን፣ ዘላቂና የመሬት መንቀጥቀጥ አደጋን የመቋቋም ከፍተኛ አቅም አላቸው።
የቅድመ-ፋብሪካ ተገጣጣሚ ቤቶችም የግንባታ ጊዜን በአጭር በማሳጠር ለፈጣን የቤት አቅርቦት ወሳኝ ሚና እየተጫወቱ ይገኛሉ። መንግሥት እነዚህን ጊዜ፣ ጉልበት እና ወጪ ቆጣቢ የሆኑ አዋጭ የግንባታ ዘዴዎች ወደ ተግባር በማስገባት ላይ በመሆኑ፣ በመጪዎቹ ጥቂት ዓመታት ውስጥ የዜጎች የዘመናት የቤት ጥያቄ ዘላቂና ዘመናዊ መፍትሔ ያገኛል ተብሎ ታላቅ ተስፋ ተጥሎበታል።
መረጃው የአዲስ አበባ ከተማ የቤቶች ልማትና አስተዳደር ቢሮ ነው፡፡
በ“ገበታ ለሀገር” ፕሮጀክት ማዕቀፍ ከደሴ ከተማ 30 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የተገነባውና እጅግ በጉጉት ሲጠበቅ የነበረው ዘመናዊው ሎጎ ሐይቅ ሪዞርት ከነገ ሐምሌ 6 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ለጎብኚዎች ክፍት ይሆናል።
በ13.3 ሄክታር መሬት ላይ ያረፈው ይህ አዲስ የቱሪዝም ፈርጥ የወሎን አስደናቂ ተፈጥሯዊ ውበት ከዘመናዊ መስተንግዶ ጋር ያቀናጀ ሲሆን፤ የሀገር ውስጥና የውጭ ሀገር ጎብኚዎች የተፈጥሮ መስህቡን እየተመለከቱ ደረጃቸውን የጠበቁ የመዝናኛና የመስተንግዶ አገልግሎቶችን እንዲያገኙ ያስችላል።
ይህ ዓለም አቀፍ ደረጃን የጠበቀ ሪዞርት ዘመናዊ ምግብ ቤቶችን፣ ማራኪ መኝታ ክፍሎችን፣ የመዋኛ ገንዳዎችንና ለዓይን የሚማርኩ አረንጓዴ ስፍራዎችን አካትቶ ይዟል። በተጨማሪም የውስጥ ለውስጥ አስፋልት መንገዶች፣ የሄሊኮፕተር ማረፊያ (Helipad) እንዲሁም በተለያዩ የፍራፍሬ ዞኖችና በደን የተከበበ በመሆኑ ለቱሪስቶች ልዩ ትውስታን የሚፈጥር ሲሆን፤ የወሎን ሕዝብ ባህላዊና ተፈጥሯዊ እሴቶች ለዓለም በማስተዋወቅ ረገድ የላቀ ሚና ይጫወታል።
በትውልዱ ዘንድ የንባብ ባህልን ለማሳደግ፣ ፍቅርንና አንድነትን ለማስተማር ታስቦ የተዘጋጀው “የንባብ ከተማ” የተሰኘው አዲስ የሕፃናት ትያትር በዛሬው ዕለት በፍላሚንጎው የአዲስ አበባ ሕፃናትና ወጣቶች ቲያትር ቤት ታላላቅ የክብር እንግዶች በተገኙበት በድምቀት ተመርቆ ለእይታ በቅቷል።
በደምሴ በየነ የተዘጋጀው ይህ ተውኔት ሕፃናትን ይበልጥ ለመሳብና የፈጠራ ክህሎታቸውን ለማሳደግ ታስቦ የተረት፣ የባህላዊ ውዝዋዜዎች፣ በሕፃናት የቀረቡ ባህላዊ ዘፈኖች እንዲሁም በተወዳጁ ተስፋ ካሳ ማይም (Mime) የታገዘ ሲሆን፤ ጥራት ባላቸው ዘመናዊ መብራቶችና ማራኪ ሙዚቃዎች ተዘጋጅቶ የቀረበ ልዩ የኪነጥበብ ድግስ ነው።
ትያትሩ ተማሪዎች ለክረምት ዕረፍት በሚወጡበት በዚህ ወቅት መዘጋጀቱ ለወላጆችና ለልጆች ትልቅ አጋጣሚ ሲሆን፤ ከዛሬ ጀምሮ ዘወትር እሁድ ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት ጀምሮ ከተለመደው ትያትር በተጨማሪ ሙዚቃ፣ ተረት እና ሕፃናትን የሚያዝናኑና የሚያስተምሩ መርሐግብሮችን በፓኬጅ መልክ አካትቶ የሚቀርብ በመሆኑ መላው ቤተሰብ መጥቶ እንዲመለከት ተጋብዟል።
በዛሬው ዕለት በአዲስ አበባ በተከናወነ ስነ ስርዓት፣ የአገሪቱን የፖሊሲ አቅጣጫ፣ የቴክኖሎጂ ሽግግር እና የሕዋ ሳይንስ ጉዞን የሚያመላክቱ ሁለት አዳዲስ መጻሕፍት በዶ/ር ይሽሩን ዓለማየሁ ተዘጋጅተው ለንባብ በቅተዋል። የምረቃ ስነ ስርዓቱ ከፍተኛ የመንግስት ሃላፊዎች፣ የትምሕርት ተቋማት አመራሮች፣ የዘርፉ ተመራማሪዎችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት በድምቀት ተካሂዷል።
ለንባብ የበቁት “Architecting the Future: A Blueprint for the Next Human Civilization” እና “Introduction to Astronautics: A Beginner's Guide” የተሰኙት መጽሐፍት፣ ኢትዮጵያ ከተለመደው የተፈጥሮ ሃብት ጥገኝነት ወጥታ ወደ ዕውቀት፣ ምርምር እና ፈጠራ መር የኢኮኖሚ ስርዓት መሸጋገር የምትችልበትን ስትራቴጂካዊ ፍንጭ የሚሰጡ መሆናቸው ተገልጿል።
“Architecting the Future” የተሰኘው የመጀመሪያው መጽሐፍ “የወደፊቱ ዓለም ምን ይመስላል?” ከሚለው የተለመደ ጥያቄ ይልቅ “ያንን ዓለም ማን ይሰራዋል? እኛስ የት መሆን ይገባናል?” የሚለውን መሰረታዊ ጥያቄ የሚያነሳ ነው። መጽሐፉ በአሁኑ ወቅት የሰውን ልጅ የዕለት ተለት ሕይወት እየቀየሩ ያሉትን እንደአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ (AI)፣ ባዮቴክኖሎጂ፣ ኳንተም ኮምፒውቲንግ፣ ሮቦቲክስ፣ ዲጂታል ኢኮኖሚ እና የጠፈር ሳይንስ ያሉ የቴክኖሎጂ አብዮቶችን በሰፊው ይተነትናል።
እነዚህ ቴክኖሎጂዎች ለሰው ልጅ ዕድልም ፈተናም ይዘው የመጡ መሆናቸውን የሚጠቁመው ይኸው መጽሐፍ፤ የወደፊቱ ዓለም በቴክኖሎጂ ብቻ ሳይሆን በስነ ምግባር፣ በሰብዓዊ ዕሴቶች፣ በፍትሕ፣ በጨዋነት እና በባለቤትነት መመራት እንዳለበት በአጽንዖት ያብራራል። በመሆኑም መጽሐፉ ለመንግስታት የፖሊሲ አቅጣጫን ለመጠቆም፣ ለዩኒቨርሲቲዎች የምርምር ራዕይ ለመስጠት፣ ለኢንዱስትሪዎች ደግሞ የፈጠራ አቅጣጫን ለማሳየት ታስቦ የተዘጋጀ መሆኑ በምረቃው ወቅት ተገልጿል።
“Introduction to Astronautics” የተሰኘው ሁለተኛው መጽሐፍ ደግሞ የሮኬት ቴክኖሎጂና የህዋ ሳይንስ የጥቂት በለጸጉ አገራት የቅንጦት ጉዳይ ብቻ አለመሆኑን በተጨባጭ ያሳያል። በአሁኑ ወቅት የሰው ልጅ በየቀኑ የሚጠቀምባቸው የስልክ ግንኙነቶች፣ ጂፒኤስ (GPS)፣ የአየር ንብረት ትንበያ፣ የውሃ ሃብት አስተዳደር፣ የከተማ ፕላኒንግ እና ብሔራዊ ደሕንነት በቀጥታ ከህዋ ቴክኖሎጂ ጋር የተሳሰሩ መሆናቸውን መጽሐፉ በምሳሌዎች ያስረዳል።
ይህ መጽሐፍ በቀላል ቋንቋ የሮኬት ሳይንስን ከመተንተን ባለፈ፣ ወጣቶች “እኛም በዚህ ዘርፍ መሰማራትና ማበርከት እንችላለን” የሚል ዕምነት እንዲያሳድሩ ለማድረግ የተጻፈ ነው። በተለይም ኢትዮጵያና አጠቃላይ አፍሪካ በዓለም አቀፉ የጠፈር ኢኮኖሚ ውስጥ ተመልካች ብቻ ሳይሆኑ ዋና ተዋናይ መሆን የሚችሉበትን ስትራቴጂካዊ መንገድ ያመላክታል።
በምረቃው ወቅት “ለምን ሁለቱ መጻሕፍት በአንድ ጊዜ ቀረቡ?” ለሚለው ጉዳይ፣ ጸሐፊው እንደገለጹት፣ “Architecting the Future” የተሰኘው መጽሐፍ “የት እንሂድ?” የሚለውን ትልቁን ራዕይና የነገውን ዓለም መልክ (ራዕዩን) ያሳያል። “Introduction to Astronautics” ደግሞ፣ “እዚያ ቦታ ላይ እንዴት እንደርሳለን?” የሚለውን እና ያንን ራዕይ ለማሳካት የሚያስፈልጉትን ሳይንሳዊና ቴክኖሎጂያዊ መሰረቶች (ትግበራውን) ያቀርባል።
የመጻሕፍቱ ዋና ዓላማ መረጃ ለመስጠት ብቻ ሳይሆን ወጣቶችን ወደ STEM (ሳይንስ፣ ቴክኖሎጂ፣ ኢንጂነሪንግ እና ማትስ) ትምህርት ለመሳብ፣ በኢትዮጵያ የሳይንሳዊ ምርምርና የፈጠራ ባህልን ለማጎልበት፣ በዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ አነቃቂ ውይይቶችን ለመፍጠር እና የፖሊሲ አውጪዎች የረዥም ጊዜ ስትራቴጂካዊ አስተሳሰብን እንዲያዳብሩ ለመርዳት ነው።
በምረቃው መርሐ ግብር ማጠቃለያ ላይ ጸሐፊው ዶ/ር ይሽሩን ዓለማየሁ ያስተላለፉት መልዕክት የአገሪቱን የወደፊት አቅጣጫ በጥብቅ የሚያሳስብ ነው። ደራሲው “የአንድ አገር ትልቁ ሀብት ወርቅ፣ ነዳጅ ወይም ሌሎች የተፈጥሮ ሃብቶች አይደሉም፤ ዕውነተኛው ሃብት የሰው አዕምሮ፣ የፈጠራ ችሎታ፣ የምርምር ባሕል እና የዕውቀት ተቋማት ናቸው። ዛሬ በዓለም ላይ የሚመረቱ ሃብቶች ሁሉ የዕውቀት፣ የምርምርና የቴክኖሎጂ ውጤቶች ናቸው። ስለሆነም የወጣቱ ትውልድ ትልቅ ሕልም እንዲኖረው፣ በሳይንስ እንዲያምን፣ በምርምር እንዲራመድ እና በፈጠራ እንዲመራ አገራዊ ጥረት ሊደረግ ይገባል። ይህ የመጽሐፍ ምረቃ የመጨረሻ ሳይሆን የአዲስ ውይይት፣ የአዲስ ምርምር እና የአዲስ ፈጠራ መጀመሪያ ነው!” ብለዋል።
የቴሌግራም ቻናልችንን በመቀላቀል የአዲስ አድማስን መረጃ ይከታተሉ…
በታሪክ ባለሙያው ስንታየሁ ኪዳኔ የተዘጋጀውና በጋዜጠኛ ይትባረክ ዋለልኝ የተሰናዳው “የአምራችነት ሰብእና” የተሰኘው አዲስ መጽሐፍ በቅርቡ ለንባብ እንደሚበቃ ታውቋል።
መጽሐፉ የኢትዮጵያን ረጅም ታሪክ መነሻ በማድረግ በሀገሪቱ ባህል፣ ዘመናዊና ባህላዊ ትምህርት፣ እንዲሁም በማኅበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ጉዳዮች ላይ ሰፊ ዳሰሳ ያደረገ ነው። ጸሐፊው ይህንን ሥራ ይፋ ለማድረግ በመስኩ ላይ በርካታ ዓመታትን የፈጀ ጥናትና ምርምር እንዲሁም ጥልቅ ፍተሻዎችን ማካሄዳቸው ተገልጿል።
ይህ አዲስ መጽሐፍ በተለይ ኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት ለገጠማት ውስብስብ ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ቀውሶች ዋና መንስኤዎች ምን እንደሆኑ በጥብቅ ሳይንሳዊ ምርምር ይፈትሻል። ከችግሮቹ ለመውጣትና መፍትሔ ለማምጣት የሚያስችሉ አቅጣጫዎችንና የመውጫ መንገዶችንም በስፋት የሚጠቁም በመሆኑ ለንባብ ሊበቃ ቀናት የቀሩትን ይህንን መጽሐፍ አንባቢዎች በትዕግሥት እንዲጠብቁ ጥሪ ቀርቧል።
የቴሌግራም ቻናልችንን በመቀላቀል የአዲስ አድማስን መረጃ ይከታተሉ…
የ2025 የአፍሪካ ምርጥ የወንዶች እግር ኳስ ዳኛ እና የፊፋ ዓለም አቀፍ ዳኛ ኡመር አብዱልከድር አርታን፣ ዛሬ በኢትዮጵያ ሶማሌ ክልል ጅግጅጋ ከተማ ሲገባ ደማቅ አቀባበል ተደርጎለታል።
ሶማሊያዊው ዳኛ በክልሉ የሚካሄደውን የዞኖች እግር ኳስ ውድድር የዋንጫ ፍጻሜ ጨዋታ በክብር እንግዳነት ለመታደምና ለአካባቢው ዳኞች የሙያ ማሻሻያ ስልጠና (ሴሚናር) ለመስጠት ጅግጅጋ መግባቱን የዜና ምንጮች ገልጸዋል። በቅርቡ ሰኔ 22 ቀን የኩዌት ፕሪሚየር ሊግ የፍጻሜ ጨዋታን በብቃት የመራው ሶማሊያዊው ዳኛ ኡመር አርታን፣ በመጪው ነሐሴ ወር በኦስትሪያ ሳልዝበርግ በፈረንሳዩ ፒኤስጂ እና በእንግሊዙ አስቶን ቪላ መካከል የሚደረገውን ታላቁን የዩኤፋ (UEFA) ሱፐር ካፕ ፍጻሜ ጨዋታ እንዲመራ መመረጡ ይታወሳል።
ዳኛ ኡመር አርታን ለ2026ቱ የዓለም ዋንጫ ከተመረጡ 52 ምርጥ ዳኞች መካከል አንዱ የነበረ ቢሆንም፣ ወደ አሜሪካ ማያሚ አየር ማረፊያ ሲደርስ በሀገሪቱ የኢሚግሬሽን ባለሥልጣናት ቪዛና መግቢያ በመከልከሉ በዓለም መድረክ ላይ ታሪክ ሳይሠራ መቅረቱ ይታወቃል።
ይህንን ዓለም አቀፍ ውዝግብና የቪዛ መከልከል ተከትሎ ከፍተኛ የሕዝብ ድጋፍና እውቅናን ያተረፈው አርታን፣ ያጋጠመውን መሰናክል በጽናት በማለፍ በአውሮፓ እግር ኳስ ማህበር ትልቅ የክብር ግብዣ ተሰጥቶታል። በጅግጅጋ የተደረገለት ደማቅ አቀባበልም ዳኛው ለአፍሪካ እግር ኳስ እያበረከተ ላለው ከፍተኛ አስተዋፅኦ የተሰጠ ትልቅ ክብር መሆኑን ዘገባዎች አመልክተዋል።
የቴሌግራም ቻናልችንን በመቀላቀል የአዲስ አድማስን መረጃ ይከታተሉ…

 አንድ የአይሁዶች አፈ-ታሪክ አለ፡፡
አንድ ኃይለኛ የመርሳት ችግር የነበረበት አይሁዳዊ ነበር፡፡ ከመርሳቱ ብዛት ማታ አውልቆት የተኛውን ልብስና ጫማ የት እንዳስቀመጠ እንኳ አያስታውስም፡፡ ልብስና ጫማውን ያስቀመጠበትን ቦታ ሲፈልግ ሁልጊዜ የጸሎት ሰዓቱ ይረፍድበታል፡፡ በፀሎት ቦታ የሚሰጠውን የቶራ ትምህርትም ጠዋት ተምሮ ማታ ይረሳዋል፡፡ እሱ ግን ከሌሎች ጓደኞቹ የተሻለ የተረዳው ይመስለዋል፡፡ “የእናንተን እውቀት ማነስ ምንም ላግዘው እንደማልችል ሁሉ፤ የእኔንም አዋቂነት ምንም ላደርገው አልችልም” እያለ ጉራውን ይነዛባቸዋል፡፡
አንድ ቀን ጠዋት ሲነሳ ልብሱን፣ ጫማዉንና ባርሜጣውን የት እንዳደረገው ጨርሶ ስለጠፋው ጠዋቱን በሙሉ እሱኑ ሲፈልግ ዋለ፡፡ ትምህርትም አመለጠው፡፡ በዚህ ምክንያት “ሁለተኛ እንዳልረሳ ዘዴ መፍጠር አለብኝ” ሲል አሰበ፡፡ ይህም ሁሌ ማታ ማታ ሲተኛ የትኛውን ልብሱን የት እንዳስቀመጠ፣ ባርኔጣውን፣ ጫማውን ወዘተ የት እንደሚያደርገው በወረቀት መዝግቦ ሊያስቀምጥ ወሰነ፡፡ በዚህ መሰረት “ኮቴ ከበሩ ጀርባ ነው፣ ሱሪዬ ወንበሩ ላይ ነው” እያለ ሁሉንም ዘርዝሮ መዘገበ፡፡
በመጨረሻም አልጋው ላይ ወጣና እንደቀልድ “እኔ ደሞ አልጋው ላይ ነኝ” ብሎ ፃፈና፣ ከትራሱ ስር አስቀምጦ ተኛ፡፡
ጠዋት ሲነሳ ወረቀቷን አውጥቶ በዝርዝሩ መሰረት ሁሉንም በየቦታው አገኘው፡፡ ከፃፈው ዝርዝር ውስጥ አንድ የመጨረሻ መስመር ግን አለ፤ “እኔ ደሞ አልጋው ላይ ነኝ” ይላል፡፡
አልጋው ላይ መኖር አለመኖሩን ለማረጋገጥ ሄዶ አየ፡፡ እሱ የለም፡፡ መኝታ ቤቱ ውስጥ በየስርቻ ሳይቀር ዞሮ አየ፡፡ ነገር ግን ራሱን ሊያገኝ አልቻለም፡፡
“እኔ ጠፍቻለሁ ማለት ነው” አለና ከቤቱ ወጥቶ ጮኸ፡፡ “ትላንት ማታ አልጋዬ ላይ መተኛቴንስ እርግጠኛ ነኝ፡፡ ዛሬ ግን የለሁም!”
ይህን ሲናገር የሰሙ ጎረቤቶቹ፤ “ትክክል ነሃ፡፡ በእርግጥ አልጋህ ላይ የለህም፡፡ ምክንያቱም አንተ እዚህ ከእኛ ጋር ነው ያለኸው፡፡” አሉና ሳቁበት፡፡
“የምለው አልገባችሁም ማለት ነው፡፡ በዝርዝሬ ላይ’ኮ ተጽፌያለሁ” አለና ወረቀቷን አውጥቶ አሳያቸው፡፡
“ጅል አትሁን አንተ ሰው፡፡ አጉል ጭንቀት ውስጥም አትግባ፡፡ ይልቅ ወደ ቤትህ ግባ” አለው አንደኛው ጎረቤቱ፡፡
“ራሴን ሳላገኝማ ወደቤቴ ልገባ አልችልም”
“እያየንህ፣ እያዋራንህ እንዴት ጠፍቻለሁ ትላለህ? መኖርህን እያየን’ኮ ነው” አሉት ሁሉም፡፡ እሱ ግን ሊሰማቸው ፈቃደኛ አልሆነም፡፡
በመጨረሻም አንድ ሰውዬ በጣም ተቆጥቶ፤ “አንተ ደደብ ሰውዬ፤ እዚህ መሆንህንና አለመሆንህን አሁኑኑ አረጋግጥልሀለሁ፡፡” ብሎ በመጥረጊያ ይቆነድደው ጀመር፡፡
“ኧረ በጣም አሳመምከኝ ጎበዝ!” ሲል ጮኸ፡፡
“አሁን ይሰማሀል፤ አይደል?” ሲል ጠየቀው፡፡
“በጣም ይሰማኛል እንጂ”
“የሚያምህ እዚሁ በመሆንህ ነው፡፡ የመታሁትም አንተን በመሆኑ ነው፡፡ አንተኑ ራስህኑ፡፡ አንተ እንዳልከው ግን ጠፍተህ ቢሆን ኖሮ ህመሙ ሊሰማህ አይችልም ነበር፡፡ አይደለም እንዴ?”
 “እውነትህን ነው፡፡ በጣም አመሰግናለሁ፡፡ እንዴት እንዳደረግኸው ባላውቅም እራሴን እንዳገኝ አድርገኸኛል፡፡ ምናልባት እኔ የተሻልኩ ሰው አልሆን ይሆናል፡፡” ሲል ራሱን ዝቅ ማድረግ ጀመረ፡፡ ቀስ በቀስ የማስታወስ ችሎታውም እየተመለሰለት መጣ፡፡
***
ሁሉን ነገር የማውቅ እኔ ነኝ፤ ከማንም ሰው እኔ እሻላለሁ፤ የማለት አባዜ ክፉ እርግማን ነው፡፡ ክፉ መገበዝ ነው፡፡ የማታ ማታ ራስን ጭምር ወደ ማጣት ያመራል፡፡ ራስን ለመፈለግ ጊዜ ያስፈልጋል፡፡ ጊዜ ከረፈደና ከመሸ በኋላ እራስን ማግኘት ዘበት ይሆናል፡፡ ይህንን መገንዘብ የጉዳዮች ሁሉ ቁልፍ ነው፡፡ ወረቀት በያዘው፣ አዋጅ በደነገገው፣ ፖሊሲ በቀረፀው፣ የትውስታ መዝገብ ቢደረደር፣ ቢገመገም ዋናው ራስ የጠፋ እስኪመስል ድረስ የግራ - መጋባትና የመወነባበድ ጣጣ ውስጥ መግባት አይቀሬ ይሆናል። ትላንት ያሉትን እንዳላሉ መሟገት፣ ትላንት ያመኑበትን በጭራሽ ዛሬ አላውቀውም ብሎ መሸምጠጥ ቀድሞውኑ ራስን ከመገበዝ የሚመነጩ ህፀፆች ናቸው፡፡ ራስን ዋርካ አሳክሎ ማየት መጨረሻው ጉቶ ማከልን መረዳት ይሆናል፡፡ ይህም የታደለና ልቡናውን የሰጠው ሰው ከተገኘ ነው፡፡ እንዲያመው እየተደረገ መኖሩን እንዲያውቅ የሚገደድ ራሱ የጠፋበት ኃላፊ፣ ባለሥልጣን ወይም መሪ ለሀገርና ለህዝብ ችግር እንጂ መፍትሄ አይሆንም፡፡ ወደዚህ አሰቃቂ ሂደት መድረስም ባንድ ስር እንደተንጠለጠለ ዛፍ የሰቀቀን አፋፍ ላይ መንጠልጠል ይሆናል፡፡
“አድረህ እይ፣ አሳድረህም እይ” እንዲሉ አስቀድሞ ታላቅነትን ከመለፈፍ ይልቅ የራስን ሚዛን ለማወቅ የሚረዳው ለራስ ጊዜ መስጠት ነው፡፡  መብሰል አለመብሰልን በጥሞና መለካት ነው፡፡ የ”አሜን ባይ” መብዛት የትክክልነት ማረጋገጫ አለመሆኑን ማጤን ነው፡፡ እኔ ያወጣሁት መርህ ትክክል ነውና ተቀበል ከማለት በፊት አንተስ ምን ይመስልሃል? ብሎ ለሌላው ሀሳብ እድል መስጠት ብልህነት ነው፡፡ ምናልባት ንጋት ላይ የቀናን መስሎ የታየን ነገር ረፋዱ ላይ ወይ ማምሻው ላይ መለወጥ አለመለወጡን በሚገባ አስተውሎ “ለአንድ ወቅት የሰጠሁት መፍትሄ መልካም ነበር፡፡ አሁን ግን ያ ዘዴ ለዚህኛው ወቅት ላይሆን ይችላል” ብሎ መጠራጠር ያባት ነው፡፡ የትላንት ጣዕም ዛሬ ቃናው መለወጥ አለመለወጡን ማጣራት እጅግ ወሳኝነት አለው፡፡ “ነብር ሲያረጅ አነር ይወልዳል” ይሏልና ከሀሳብ ማርጀት፣ ከፖሊሲ ማርጀት፣ ከፕሮግራም መጣረስ ጋር የሚመጡትን ከሁኔታዎች ጋር የማይጣጣሙ እምነቶች አላየሁም አልሰማሁም ብሎ የዱሮውን ሃሳብ እኝኝ ብሎ መያዝ ተገቢ አይደለም፡፡ አገርና ዓለም ተቀበለውም አልተቀበለውም እኔ ያሰብኩት ጋ ካልደረስኩ ፍሬን አልይዝም - አንዳች የሚያቆመኝ ኃይልም ሊኖር አይችልም ብሎ ግትርነትን ማወጅ፣ ካፈርኩ አይመልሰኝ እንጂ ሌላ ፍሬ የምናፈራበት መላ አይደለም፡፡
የተመኘነው፤ ያለምነው ያቀድነውና የተለምነው ሁሉ ሙሉ በሙሉ ላይሳካ ይችላል ከሚለው እሳቤ ጀምሮ ከመሰረቱስ ሙሉ በሙሉ ስህተት ቢሆን እስከ ማለት ድረስ ለማሰላሰል ዝግጁና ደፋር መሆን ተገቢ ነው፡፡ ያማረውና የተሳካው ሁሉ የእኔ ድካም ፍሬ፣ የተሳሳተውና የተበላሸው ሁሉ የጠላቴ ሴራ ውጤት፤ ብሎ መፈረጅ የኋላ ኋላ ራሱ እንደጠፋበት ሰው መደነጋገርንና በአደባባይ “ራሴን አፋልጉኝ” ማለትን ያስከትላል፡፡
ከቶውንም የሌሎችን ድካም ለራስ ማድረግ ከአንድ ጀንበር በላይ ሊሸሸግ የሚችል ነገር አይደለም። “ያላረባ ልኳንዳ አራጅ ዐይን የሆነውን ብልት ይበላል” እንደሚባለው በሌሎች ጥናት መኩራራት፤ በሌሎች ሪፖርት ላይ ፈርሞ ብቻ መመስገን፤ በሌሎች ጫንቃ የተሰራን ስራ የእኔ ነው ማለት፤ ለሥራም፤ ለእድገትም፣ ለራስም ደግ አይደለም፡፡ አድሮ ያጋልጣልና!
በሲቪል ሰርቪስ መርሆዎች መሻሻል ብቻ መልካም አስተዳደር አይመጣም፡፡ ሰው ይፈልጋል፡፡ መርሆዎችን ከልቡ ሊተገብር የቆመ ሰው ይፈልጋል፡፡ ፍትሕ ርትዕ የሰፈነባት አገርን የሚያመላክት በርካታ አቅጣጫ ሊነደፍ ይችላል፡፡ ግን የወረቀት ስራ ብቻ ነው፡፡ ሰው ይፈልጋል፡፡ በትላንቱ አባያ በሬ አዲስ መሬት ልረስብህ ቢሉት ትርፉ ጅራፍ ማጮህ እንደሚሆን ጥርጥር የለውም፡፡ ወደ ባህልነት ሊቀየር አንድ ሀሙስ የቀረው ሙሰኝነት ምንም ያህል የጠበቁ አናቅጽትና ህግጋት ቢጠቀሱለት፤ ተግባራዊ ትርጓሜ የሚሰጣቸው እጁን የታጠበና ልቡን ያፀዳ ሰው ብቻ ነው፡፡
አለበለዚያ “የወረት ውሻ ስሟ ትደነቂያለሽ ነው” ከሚባለው ፈሊጥ የዘለለ ነገር አይገኝም፡፡ በእርግጥም በተጎሰመው ነጋሪት፣ በተላለፈው አዋጅ፣ በብራና በተከተበው ህግና መመሪያ ጥናቱን ያስጠናውን ክፍል ለማስደሰት ይቻላል፡፡ ተግባሩ ግን ከፍተኛ የሰው ኃይልና ልባዊ ህዝባዊ ተሳትፎ እንዲኖር የማድረግን ብርቱ ጥረት የሚጠይቅ ተልዕኮ ነው፡፡ የሃገራችን የዘወትር ህመም፤ ያማረ እቅድና እንከን - አልባ የተባለ የወረቀት ስራ በተነደፈ ቁጥር፤ የተፃፈው ሊቀደድ እንደሚችል የታቀደው ሽባ ሆኖ ሊቀር እንደሚችል ዘንግቶ፣ ከአፍ አፍ እየተቀባበሉ በየመዋቅሩ አሸንዳ የድል ብስራት መለፈፍ፣ ነገ ያለአንዳች ተግባር በነባቤ - ቃልነት ብቻ ሊቀር እንደሚችልና ለከፋ ችግር ሊያጋልጥ እንደሚችል አለመገንዘብና ተዘናግቶ ማዘናጋት ነው፡፡ “የአሬራ ጥጋብ የሚመጣውን ክረምት ያስረሳል” እንደሚባለው መሆኑ ነው!

Page 2 of 810