Administrator
Monday, 03 November 2025 16:24
የቀድሞው የእግር ኳስ ኮከብ ዴቪድ ቤካም የግብርና ሥራ ጀመረ
ለዓመታት በዘመናዊቷ ለንደን ከተማ ሕይወቱን የመራው ዝነኛው እንግሊዛዊ ዴቪድ ቤካም አሁን ላይ በገጠራማዋ የኮትስዎልድስ መንደር በሚገኘው መኖሪያ ቤቱ ዙሪያ የግብርና ሥራን እያስፋፋ ነው።
ዛፎችን በመትከል፣ የአትክልት ስፍራዎን በመንከባከብ፣ ዶሮዎችን በማርባት እና ንብ በማነብ ሥራ ላይም ተሰማርቷል።
የግብርና ሥራው ላይ ቤተሰቡም እየተሳተፈ መሆኑን ሜትሮ የተሰኘው ሚዲያ ዘግቧል።
Published in
ስፖርት አድማስ
Tagged under
Sunday, 02 November 2025 06:26
ስለ አደባባይ ሐውልቶቻችን ሥነ ጥበባዊ ወግ
የኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት 10ኛውን የወር ወንበር በድምቀት አከናወነ።
በአስረኛው የወር ወንበር
"ስለ አደባባይ ሐውልቶቻችን ሥነ ጥበባዊ ወግ"
የኢትዮጵያ ቤተ መዛግብትና ቤተ መጻሕፍት አገልግሎት (ወመዘክር) ማህበራዊ፣ፍልስፍናዊ፣ታሪካዊ፣ጥበባ
ዊና ሀገራዊ ጉዳዮችን በማንሳት ጥልቅ ውይይት እና የሀሳብ ልውውጥ የሚደረግበት የወር ወንበር አስረኛ መርሐግብሩን ጥቅምት 22 ቀን 2018 ዓ.ም በተቋሙ ብላታ መርስዔ ኃዘን ወልደ ቂርቆስ አዳራሽ አከናውኗል።
የወሩ ወንበር "ስለ አደባባይ ሐውልቶቻችን ሥነ ጥበብ ወግ" በሚል ርዕስ ሲሆን የውውይት መነሻ ሀሳብ
ያቀረቡት በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የአለ ፈለገ ሰላም የሥነ ጥበብ ትምህርት ቤት ዲን ሰዓሊ አገኘሁ አዳነ ናቸው።
የአደባባይ ሐውልቶቻችን አሠራራቸው፣በታሪክ ውስጥ ያለፉበት መንገድ፣የታለመላቸውን ሀሳብ ዓላማ
የማስተላለፍ አቅማቸው፣ የተሰሩበት ዓላማ፣የፈረሱ ሐውልቶች፣በአደባባይ በቆሙ ሐውልቶቻችን ላይ የተነሱ ጉዳዮች እና ስለሐውልቶቹ ምን ተባለ የሚሉትን ሰዓሊ አገኘሁ አዳነ በገለጻቸው ከዳሰሷቸው ነጥቦች የሚጠቀሱ ናቸው።
የዕለቱ ታዳሚያን ንቁ ተሳትፎ ጎልቶ በወጣበት የወር ወንበር፤የተቋሙ ዋና ዳይሬክተር አቶ ሠርፀ ፍሬስብሐት መርሐግብሩን ከዚህ በላቀ መልኩም ለማስቀጠል ተቋሙ እንደሚሰራ እና የወር ወንበር ሁሌም በወሩ የመጨረሻ ሳምንት ቅዳሜ ላይ የሚዘጋጅ በመሆኑ ታዳሚያን ይገኙ ዘንድ የክብር ጥሪን አስተላልፈዋል።

Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና
Tagged under
Tuesday, 28 October 2025 00:00
ሎሚ
፩) ሎሚ የጉሮሮን ኢንፌክሽን ከሚከላከሉ ፍራፍሬዎች አንዱ ሲሆን የፀረ ባክቴሪያ ሀይል ስላለው በሻይ መልክ መጠጣት ከፍተኛ ጥቅም ይሠጣል።
፪) የሎሚ ጭማቂ የምግብ አለመፈጨትንና የሆድ ድርቀትን ይከላከላል።
፫) በምግብ ውስጥ ትንሽ ጠብታ ሎሚ ጨምሮ መጠቀም ደምን ያጣራል።
፬) ጥሩ የዕቃ ማፅጃ በመሆንም ያገለግላል።
፭) የሎሚ ጭማቂ በብርድ፣ በሳልና በትኩሳት ለሚሰቃዩ ሰዎች መድሀኒት ነው። እንዲሁም ትኩሳት በሚኖር ወቅት ቶሎ ቶሎ እንዲያልበን በማድረግ ያስታግስልናል።
፮) የጥርስ ህመም በሚያጋጥምበት ጊዜ የሎሚ ጭማቂ በህመሙ ቦታ ላይ በማድረግ እንደ ማስታገሻነት መጠቀም ይቻላል።
፯) በሎሚ ጭማቂ ድድን ማሸት ከድድ መድማት ችግርና ከመጥፎ የአፍ ጠረን ይታደጋል።
፰) ከውሀ ጋር የተቀላቀለ የሎሚ ጭማቂ መጠጣት ለኩላሊት ጠጠር እጅግ በጣም ጠቃሚ ነው።
፱) የሎሚ ጭማቂ በተቃጠለው የሰውነታችን ቁስል ላይ በማድረግ ጠባሳ እንዳይኖር ለማድረግ ያስችላል።
፲) የሎሚ ጭማቂ ውስጣዊ መድማትን ይከላከላል። ምክንያቱ ሎሚ ፀረ ጀርምና ፀረ ባክቴሪያ ባህሪ ስላለው ነው። ስለሆነም የአፍንጫ መድማትን ለመከላከል በሎሚ ጭማቂ የተነከረ ጥጥ በአፍንጫ ቀዳዳ ውስጥ ከተው ለትንሽ ደቂቃዎች ማቆየት ይመከራል።
፲፩) ሎሚ ደምን የማጣራት አቅም ስላለው እንደ ወባና አተት ያሉ በሽታዎችን ይከላከላል።
፲፪) ሎሚ የፀረ ጀርምና ፀረ ባክቴሪያ ባህሪ ስላለው እርጅናን፣ የቆዳ መሸብሸብና ቆዳ ላይ ያሉ ትንንሽ ጥቁር ነጠብጣቦችን ያስወግዳል።
፲፫) የፀሀይ ጨረርን ለመከላከል የሎሚ ጭማቂ ፊትን መቀባት ጠቃሚ ነው።
፲፬) የሎሚ ጭማቂ ከማርና ውሀ ጋር በመቀላቀል መጠጣት ጥርት ያለ የፊት ቆዳ እንዲኖረን ያደርጋል።
፲፭) የሎሚ ጭማቂ የሰውነት ክብደትን ለመቀነስ ይረዳል።
፲፮) ሎሚ በቫይታሚን ሲ የበለፀገ ስለሆነ የአስምና የመተንፈሻ አካላት ችግር ላለባቸው ሰዎች በጣም ጠቃሚ ነው።
፲፯) ሎሚ በውስጡ ፖታሲየም ስላለው ጭማቂውን መጠጣት የልብ ህመምን ለማስታገስ ይጠቅማል።
፲፰) ከፍተኛ የደም ግፊትን፣ ማዞርና ማቅለሽለሽን በመቆጣጠር አእምሮና ሰውነታችን ዘና እንዲል ያደርጋል።
፲፱) የራስ ቆዳ አናትን የሎሚ ጭማቂ መቀባት እንደ ፎረፎር፣ የፀጉር መነቃቀልና ከራስ ቅል ጋር የተያያዙ ችግሮችን ለመከላከል ይጠቅማል። እንዲሁም ፀጉራችን አንጸባራቂ እንዲሆን ያደርጋል።
የቴሌግራም ቻናልችንን በመቀላቀል የአዲስ አድማስን መረጃ ይከታተሉ…
.
Published in
ዋናው ጤና
Tagged under
Friday, 31 October 2025 09:40
የዋሲሁን በላይን "አልንበረከክም"
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና
Tagged under
Friday, 31 October 2025 08:11
የኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተ መጻሕፍት አገልግሎት ነገ ጥቅምት 22/2018 ዓ.ም ከቀኑ 10፡00 ሰዓት ጀምሮ የማይቀርበት የሥነ ጥበብ ድግስ አዘጋጅቷል፡፡
በዝግጅቱ ጥሪ የተደረገላችሁ እንግዶች፣የጥበብ ባለሙያዎች እንዲሁም የሚድያ አካላት በቦታው በመገኘት ዝግጅቱን በመዘገብ ለሕዝቡ እንድታደርሱ ከወዲሁ በአክብሮት እንጋብዛለን፡፡
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና
Tagged under
Thursday, 30 October 2025 13:27
ከ100 በላይ ዓለማቀፍ የእንስሳት ሃብት ተዋናዮች የሚሳተፉበት የንግድ ትርዒት ተከፈተ
* ከ5 ሺሕ በላይ ሰዎች ይገበኙታል ተብሎ ይጠበቃል
ከ14 አገራት የተውጣጡ ከ100 በላይ ዓለም አቀፍ የእንስሳት ሃብት ዘርፍ ተዋናዮች የሚሳተፉበት የንግድ ትርዒት ዛሬ በአዲስ አበባ፣ ሚሊኒየም አዳራሽ መካሄድ ጀምሯል። በዚህ የንግድ ትርዒት ላይ ከ5000 በላይ የኢትዮጵያ፣ የምስራቅ አፍሪካና ዓለም አቀፍ አገራት ጎብኚዎች እንደሚጠበቁ ተነግሯል።
በዚሁ የንግድ ትርዒት ስር፣ 14ኛው የኢትዮ ፖልተሪ ኤክስፖ (ኢትዮቼከስ)፤ 10ኛው የአፍሪካ እንሰሳት ዓውደ ርዕይና ጉባዔ (አሌክ) እንዲሁም 5ኛው የአፒካልቸር እና አኳካልቸር ኢትዮጵያ ዓለማቀፍ የንግድ ትርዒትና ዘንድሮ ለሁለተኛ ጊዜ የሚካሄደው የባዮ ኢነርጂ የንግድ ትርዒት በአንድነት የሚከናወኑ ሲሆን፣ በንግድ ትርዒቱ ላይ ጥራት ያላቸው የዘርፉ ዋነኛ አንቀሳቃሾች እንደሚሳተፉበት ተገልጿል።
የፕራና ኢቨንትስ የፕሮጀክት ስራ አስኪያጅ ሜሮን ስሎሞን እንደተናገሩት፣ ባለፉት ዓመታት የተካሄዱት ዓውደ ርዕይና ጉባዔዎች ለዶሮ፣ ዕንቁላል፣ ወተትና ስጋ ንዑስ ዘርፎች ዕድገትና ልማት ከፍተኛ አስተዋጽዖ አበርክተዋል። አክለውም፣ "እነዚህ ሁነቶች ለዘርፉ ባለሞያዎችና ለንግዱ ማሕበረሰብ ትልቁ መሰባሰቢያ በመሆናቸው የገበያ ትስስር በመፍጠር፣ አዳዲስ ቴከኖሎጂዎችን በማስተዋወቅ፣ የዕውቀት ሽግግርን በማምጣት እንዲሁም የኢንቨስትመንት ዕድሎችን በማስተዋወቅ ለዘርፉ ልማት ያላቸውን ከፍተኛ አስተዋጽዖ ማረጋገጥ ችለዋል" ሲሉ ተናግረዋል፡፡
ፕራና ኤቨንትስና መቀመጫውን ሱዳን ባደረገው አጋሩ ኤክስፖ ቲም ትብብር የሚዘጋጀው ሁሉን-አቀፍ የእንስሳት እርባታ ቴከኖሎጂ፣ ግብዓት እና መፍትሔዎች ላይ ትኩረት የሚያደርገው ዓለም አቀፉ የንግድ ትርዒት፣ የእንስሳት ሃብት የገበያ ስንሰለቶች ላይ ያሉ የኢንቨስትመንት ዕድሎችን የገበያ ትስስር ለመፍጠር እንዲሁም የዕውቀትና የቴከኖሎጂ ሽግግር ለማምጣት ኔዘርላንድን ጨምሮ ከ14 አገራት የተውጣጡ ከ100 በላይ የዘርፉ ድርጅቶች እንደሚሳተፉ ለማወቅ ተችሏል።
በኢትዮጵያ ባሕላዊ የዶሮ እርባታ እስካሁን በስፋት የሚዘወተር ልምድ መሆኑን በመድረኩ ላይ ሲጠቆም፣ ዘመናዊ የዶሮ እርባታን በማስፋፋት የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በሚደረገው ጥረት ውስጥ አስፈላጊውን አስተዋፅኦ ለማድረግ የሚዘጋጅ ብቸኛው የዘርፉ ዓለም አቀፍ ሁነት የኢትዮ ዶሮ ኤክስፖ መሆኑም ተጠቅሷል። እንዲሁም የአፍሪካ የእንስሳት ሃብት ዓውደርዕይና ጉባዔ ደግሞ፣ ኢትዮጵያ ከፍተኛ የእንስሳት ሃብት ባለቤት መሆኗ ባያጠራጥርም፣ በዘርፉ ያላት ምርታማነትና የነፍስ ወከፍ ፍጆታ ከዓለም ዝቅተኛ መሆኑን ግምት ውስጥ በማስገባት፣ የወተት እና የስጋ ዘርፉን በዘመናዊ መልክ ለማሳደግ ትኩረት ተሰጥቶ የሚሰራበት "መድረክ ነው" ተብሏል።
የንግድ ትርዒቱ ከጥቅምት 20 እስከ 22 ቀን 2018 ዓ.ም. ድረስ ለጎብኚዎች ክፍት ይሆናል።

Published in
ዜና
Tagged under
Thursday, 30 October 2025 11:22
አቶ የማነ ገ/መስቀል ኢትዮጵያ በወደብ ጉዳይ ስለያዘችው አቋም ምን አሉ?
የኤርትራ መንግሥት ቃል አቀባይ አቶ የማነ ገ/መስቀል፣ የኢትዮጵያው ገዥ ብልጽግና ፓርቲ በባሕር በር ጉዳይ ላይ የሚከተለው "አምታች የኾነ አካሄድ" በቀጠናው ጦርነት ሊቀሰቅስ ይችላል በማለት ከሰሞኑ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት አስጠንቅቀዋል።
የኢትዮጵያ ጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኤታማዦር ሹምና ሌሎች የአገሪቱ ከፍተኛ የጦር መኮንኖች በኤርትራ ላይ "የጦርነት ዛቻ" ማሰማት ቀጥለዋል በማለት የከሠሡት ቃል አቀባዩ፤ በሌላ በኩል ደሞ ብልጽግና ኢትዮጵያን ከምጽዋ፣ አሰብና ከጅቡቲዋ ታጁራ ወደብ ጋር የሚያገናኝ የባቡር ሐዲድ ለመገንባት እንዳቀደ በመግለጽ፣ "አምታች አካሄድ" ይከተላል በማለት ተችተዋል።
ቃል አቀባዩ በዚህ ሳምንት ጠ/ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ በፓርላማ በወደብ ጉዳይ ከተናገሩ በኋላ ቃል አቀባዩ በሰጡት ምላሽ፤ ብልጽግና ፓርቲ በአሰብ ወደብ ዙሪያ የሚያሠማው "ቅዠት" እየተባባሰ ሄዷል ብለዋል፡፡
አቶ የማነ፣ ማክሰኞ'ለት በኢትዮጵያ ፓርላማ ውስጥ የተሠማው ትርክት፣ "ከተቻለ በድርድር፤ ካልተቻለ በወታደራዊ ወረራ የአሰብ ወደብ ባለቤት እንኾናለን" የሚል ይዘት አለው ሲሉ ገልጸዋል፡፡ የቅኝ ግዛት ትርክት ሲቃኝ የኖረው ማራኪ በሚመስሉ አመክንዮዎች ወይም ሕዝቦችን የማሠልጠን ተልዕኮ በሚል ምክንያት ነበር ያሉት ቃል አቀባዩ፤ "ሞኛሞኝ የሆነው የብልጽግና ትርክት ግን በዘመናዊ ታሪክ ተሠምቶ አያውቅም" ብለዋል።
(ዋዜማ)

Published in
ነፃ አስተያየት
Tagged under
Thursday, 30 October 2025 11:21
የትግራዩ ጦርነት 10. 8 ቢ. ዶላር ማህበራዊ ውድመት አድርሷል - ኮሚሽኑ
የትግራይ የዘር ማጥፋት ኮሚሽን፣ የትግራዩ ጦርነት ያስከተለው ማኅበራዊ ውድመትና ኪሳራ 10 ነጥብ 8 ቢሊዮን ዶላር እንደሚገመት በጥናት ማረጋገጡን አስታውቋል።
ኮሚሽኑ ጦርነቱ ከፍተኛውን ውድመት ያደረሰው በትምህርት ዘርፉ ላይ መኾኑን ይጠቅሳል።
ሪፖርቱ፣ የኤርትራ ሠራዊት በትምህርት፣ በጤና ሥርዓቶች፣ በቅርሶች፣ በታሪካዊ ሕንጻዎች፣ በእደ ጥበባትና በታሪካዊ ቁሳቁሶች ላይ ከ38 እስከ 56 በመቶ የሚደርስ ጉዳት አድርሷል ብሏል።
ባንጻሩ የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት፣ በቁጠባና ብድር ተቋማት፣ በኅብረት ሥራ ማኅበራት፣ በአነስተኛ ማኅበራዊ አገልግሎት ሠጪ ተቋማት ላይ የ27 ነጥብ 2 በመቶ ጉዳት ማድረሱን ኮሚሽኑ ገልጧል።
[ዋዜማ]
Published in
ዜና
Tagged under
Thursday, 30 October 2025 11:15
የአቤል ተስፋዬ (ዘ ዊክንድ) የሃብት መጠን 600 ሚ. ዶላር ደርሷል
የዝነኛው አቀንቃኝ ዘ ዊክንድ (አቤል ተስፋዬ)፣ የተጣራ የሀብት መጠን በአራት ዓመታት ውስጥ በሦስት እጥፍ አድጎ 600 ሚሊዮን ዶላር መድረሱ ተዘገበ፡፡
ሰለብሪቲ ኔት ዎርዝ ድረ-ገጽ እንደገለጸው፤ የዚህ ዓለማቀፍ ድምጻዊ አጠቃላይ ሀብት እ.ኤ.አ. በ2021 ከነበረበት 200 ሚሊዮን ዶላር በአራት ዓመታት ወደ 600 ሚሊዮን ዶላር አሻቅቧል - የ400 ሚሊዮን ዶላር ጭማሪ በማሳየት፡፡
የድምጻዊው "Blinding Lights"ን የመሳሰሉ ተወዳጅ ሥራዎቹ በበይነመረብ የሙዚቃ ማሰራጫ መድረኮች በቢሊዮኖች የሚቆጠሩ ጊዜያት መደመጣቸው ለገቢው መጨመር የጎላ አስተዋጽኦ ማድረጋቸው የተነገረ ሲሆን፤ እ.ኤ.አ. በ2024 ከስፖቲፋይ ብቻ ከ50 ሚሊዮን ዶላር በላይ ገቢ ማግኘቱ ተጠቁሟል፡፡
በተጨማሪም ዝነኛው አቀንቃኝ ከአዳዲስ፣ ፑማና ሌሎች ታላላቅ ኩባንያዎች ጋር ባለው የሥራ ውል ከፍተኛ ገቢ እንደሚያገኝ መረጃዎች ይጠቁማሉ፡፡
ዘ ዊክንድ በተለያዩ የበጎ አድራጎት ሥራዎች ላይ በስፋት እንደሚሳተፍም ይታወቃል፡፡
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና
Tagged under

