በአሁኑ ሰዓት በአሜሪካ እየተካሄደ በሚገኘው የዓለም ሮቦቲክስ ሻምፒዮን ላይ ኢትዮጵያውያን ተማሪዎች እየተሳተፉ እንደሚገኙ ለማወቅ ተችሏል።
ለዚህ የዓለም ሮቦቲክስ ሻምፒዮን ኢትዮጵያውያን ተማሪዎችን ይዘው ወደ አሜሪካ የተጓዙት የኢትዮ ሮቦ ሮቦቲክስ የትምህርትና ውድድር ማዕከል መሥራችና ዋና ሃላፊ አቶ ሰናይክሪም መኮንን ናቸው።
በአሜሪካው ውድድር ላይ ለመሳተፍ የተመረጡት ተማሪዎች በቅርቡ እዚህ አዲስ አበባ በኢሊሌ ሆቴል በተካሄደ የአፍሪካ ሮቦቲክስ ሻምፒዮና የላቀ ውጤት ያመጡ ሲሆን፤ በቪዛ መዘግየትና በቲክኒካል ጉዳዮች ከጉዞው የቀሩም ተማሪዎች እንዳሉ ታውቋል።
Published in
ዜና