Thursday, 04 April 2024 17:12

"ሆኖ መገኘት” በዱባይ ቅዳሜ መጋቢት 28 / አፕሪል 6 2024 ከምሽቱ 5:30 – 7:30 በበገና ሬስቶራንት አዳራሽ ይመረቃል::

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

ይህ ‹‹ሆኖ መገኘት፤ እኔም ኃይሌ ነኝ›› የተሰኘ መጽሐፍ በኢትዮጵያ የድርጅቶች አገልግሎት ልህቀትን ለማሳደግ በማሰብ የተደረገ የእውቀት ሽግግር ጥረት ነው፡፡ ይህ መጽሐፍ ወደ ልህቀት የሚደረግን ጉዞ የሚያግዝ ብቻ አይደለም፤ ይልቁንም መንገድንም የሚያመላክት እንጅ፡፡

‹‹ሆኖ መገኘት›› ማዕከል የሚያደርገው የአገልግሎት ልህቀት ከፍ እያለ በተግባር እየታየበት ያለውን ኃይሌ ሪሶርቶችና ሆቴሎች ሲሆን የሥረ ነገር ማጠንጠኛውም ራሱ ሆኖ መገኘትን ያሳዬን ኃይሌ ገብረ ሥላሴ ነው፡፡ መጽሐፉ የሥራ ባህል ምን ያህል ወሳኝ መሆኑን አጽኦት የሚሰጥ ከመሆኑም በላይ የስራ ባህል ምንነትን እና ተግባራትን ከመቅረጽ አንጻር ያለውን ሚና ያትታል፡፡

ሆን ተብሎ ቢሆንም እና ባይሆንም ባህል እያንዳንዱ ከባቢ ላይ ተጽዕኖውን ያሳርፋል፤ የግለሰቦች ይሁን የድርጅቶችንም ግብር እና ምግባር ይቀርጻል፡፡ ይህን ሀቅ ስንቅ አድርጎ በመያዝ ኃይሌ ሪሶርቶችና ሆቴሎች  ከቃል በላይ የሆነ በተግባርም የተገለጸ አዲስ ባህልን ለመፍጠር ችሏል፡፡

በዚህ መጽሐፍ የምንነግራችሁ ንድፈ ሐሳብ አይደለም፤ ይልቁንም እየተኖረ ያለ እና በተግባር የተገለጸን እውቀት እንጅ፡፡ ይህም እውቀት የጋራ የሆነ እንጅ ለጥቂቱ ተገልጦ ብዙኃኑ ያላገኙት ትንቢት አይደለም፡፡ ለውጡም ከተግባርዎ፣ ከምግባርዎ፣ ከሥነ ልቦናዎም ዘንዳ የሚታጨድ እሸት ነው፡፡ ስሊዚህም እንዲህ እንላለን ‹‹ማንም ቢሆን ልክ እንደ ኃይሌ ማሰብን መልመድን እና መሥራትን ይችላል›› ስለዚህም ‹‹እኔም ኃይሌ ነኝ›› ፍልስፍና የስኬት ቁልፍ ለእርስዎ እነሆ!

Read 547 times