ወመዘክር አዲስ ያስገነባውን ህንፃ የፊታችን ቅዳሜ ያስመርቃል
• የተቋሙ የ80ኛ ዓመት ክብረ በዓልም ይከበራል ተብሏል
የኢትዮጵያ ቤተ-መዛግብትና ቤተ-መጻሕፍት አገልግሎት ያስገነባውን ባለ 13 ወለል የቤተመዛግብት ሕንጻ የፊታችን ቅዳሜ የካቲት 16 ቀን 2016 ዓ.ም እንደሚያስመርቅ ተገለጸ።
ከህንፃው ምርቃት ጎን ለጎንም ተቋሙ የተመሰረትበት የ80ኛ ዓመት ክብረ በዓልም በአንድ ላይ ይከበራል ተብሏል፡፡
እነዚህን ሁነቶች ምክንያት በማድረግ በተቋሙ ተመዝግበውና ተጠብቀው የሚገኙና በሌሎች ተባባሪ ተቋማት እጅ የሚገኙ የጽሑፍ ቅርሶች አውደርዕይና ሌሎች ተቋሙን ሊያስተዋውቁ የሚችሉ ክንውኖች እንደሚካሄዱ ለማወቅ ተችሏል፡፡
ዝግጅቶቹ ከእሁድ የካቲት 17 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ ለእይታ ክፍት እንደሚሆኑ ተነግሯል፡፡
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና