እኛ ስንከፋ ፤
ምድሩን ቆርቆር
አንገት ደፍተን ቆፈር ቆፈር ...
ጌቶች ሲከፋቸው ፤
እኛን ኮርከም ኮርከም
በ፩ ላይ ወግነው ፥ ከፀሀይ ከሀሩሩ ጋር ።
አቤት ብንል ለ “ ማ “ ?
አካላችን ቀልጦ
ተስፋችን ተውጦ ፤
እንባና ደማችን በ፩ ጅረት ሲፈስስ
ባመንነው መዶሻ አናታችን ሲፈርስ ።
ይግባኝ ብንል ለ “ ማ “
ሠማዩ እንዲታረስ ፤
ዳኛው ችሎት መጥቶ በንጉሱ ፈረስ ።
የአብፀጋ ተመስገን /maddbn
Published in
የግጥም ጥግ