አትሌት ታምራት ቶላ በኒው ዮርክ በተካሄደው የማራቶን ውድድር አሸናፊ መሆን ችሏል፡፡
አትሌት ታምራት ውድድሩን ለማጠናቀቅ 2 ሰዓት ከ4 ደቂቃ ከ58 ሰኮንድ የፈጀበት ሲሆን፤ የገባበት ሰዓትም በኒው ዮርክ ማራቶን ውድድር ታሪክ አዲስ ክብረ ወሰን ሆኗል፡፡
በውድድሩ ሌላኛው ኢትዮጵያዊ አትሌት ሹራ ቂጣታ ሶሰትኛ ደረጃን ይዞ አጠናቋል::
በሴቶቹ በኩል አትሌት ለተሰንበት ግደይ የኒው ዮርክ ማራቶን ውድድር ሁለተኛ በመሆን ስታጠናቅቅ፤ ኬኒያዊቷ አትሌት ሄለን ኦቢሪ አንደኛ በመውጣት ውድድሩን አሸንፋለች::