የደራሲ ይፍቱሥራ ምትኩ ሁለተኛ የልቦለድ ስራ የሆነው ”ወድቆ የተገኘ ሐገር” የተሰኘ መጽሐፍ ባለፈው ሳምንት ለንባብ በቅቷል:: መጽሐፉ 110 ገፆች ያሉት ወጥ ልቦለድ መሆኑን ደራሲዋ ተናግራለች፡፡
“ወድቆ የተገኘ ሐገር” መቼቱን በ1990ዎቹ መጀመሪያ በአገራችን በተካሄደው የኢትዮ -ኤርትራ ጦርነት ላይ በማድረግ የተጻፈ ልብወለድ ሲሆን፤ ታሪኩ ከአስከፊ ጦርነት የተመለሰ ታዳጊን ህይወትና አጠቃላይ የቤተሰቡን ኑሮ ያስቃኛል::
ደራሲዋ ከዚህ ቀደም “በተለይ አስራ አንደኛው” የተሰኘ ልቦለድ መጽሐፍ ለንባብ ማብቃቷ ይታወሳል::
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና