Saturday, 09 September 2023 00:00

“ወድቆ የተገኘ ሐገር” መጽሐፍ ለንባብ በቃ

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

የደራሲ ይፍቱሥራ ምትኩ ሁለተኛ የልቦለድ ስራ የሆነው ”ወድቆ የተገኘ ሐገር” የተሰኘ መጽሐፍ ባለፈው  ሳምንት ለንባብ በቅቷል:: መጽሐፉ 110 ገፆች ያሉት ወጥ ልቦለድ መሆኑን ደራሲዋ ተናግራለች፡፡  
“ወድቆ የተገኘ ሐገር” መቼቱን በ1990ዎቹ መጀመሪያ በአገራችን በተካሄደው  የኢትዮ -ኤርትራ ጦርነት ላይ በማድረግ  የተጻፈ ልብወለድ ሲሆን፤ ታሪኩ ከአስከፊ ጦርነት  የተመለሰ ታዳጊን ህይወትና አጠቃላይ የቤተሰቡን ኑሮ  ያስቃኛል::
ደራሲዋ ከዚህ ቀደም “በተለይ አስራ አንደኛው” የተሰኘ ልቦለድ መጽሐፍ ለንባብ ማብቃቷ ይታወሳል::

Read 2078 times