Saturday, 12 August 2023 00:00

“ጦርነት መፍትሄ አይኾንም፤ ከትናንት እንማር”

Written by 
Rate this item
(0 votes)

”--ጦርነት መፍትሄ አይኾንም፤ ከትናንት እንማር፤ ችግሮችን በውይይት እንፍታ፤ በሀገራችን ሰሜናዊ ክፍል ለሁለት ዓመታት የተካሄደው ጦርነት ካደረሰብን ዘርፈ ብዙ ችግሮች ገና በቅጡ እንኳ ባላገገምንበት በዚህ ወቅት፣ ዳግም ወደ ሌላ መጠነ ሰፊ የእርስ በርስ ግጭት መግባት፣ በሕዝባችን ላይ የሚያደርሰው ማኀበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ስነ ልቡናዊ ጉዳት በእጅጉ የሚያሳስብ ነው። ጦርነት ከፍተኛ መጠን ያለው ሰብኣዊ እልቂትንና ቁሳዊ ውድመትን ከማስከተል በቀር፣ ለችግሮቻችን መፍትኄ እንደማያስገኝ ከቅርብ ጊዜው ተሞከሯችን መማር አለመቻላችን እጅግ አሳዛኝ ነው። በሀገር ውስጥ የሚካሄድ ጦርነት፣ የሀገር አንድነት ፀንቶ የቆመባቸውን የእሴት አምዶች በማፍረስ፣ የሕዝባችንን አንድነት የሚንድ በመኾኑ፣ ሁሉም አካላት ሁኔታውን ከማባባስ ተቆጥበው፣ ወደ ውይይት መምጣት የሚቻልበትን መላ ያፈላልጉ፡፡ የሚመለከታቸው አካላት በሙሉ፤ እጅግ አውዳሚና አክሳሪ ከኾነው ጦርነት፣ የችግር መፍትኄን ከመጠበቅ ይልቅ፣ በአስቸኳይ ወደ ውይይት ይምጡ።--”
(የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ሰሞኑን ካወጣው መግለጫ የተወሰደ)

Read 1008 times