Saturday, 29 July 2023 11:26

ከራስህ ጀምር!

Written by 
Rate this item
(0 votes)

 በዌስት ሚኒስትር አቤይ፣ በአንድ የአንጀሊካን ጳጳስ መቃብር ላይ ተከታዮ ሃሳብ ሰፍሯል፡፡ ወጣትና ነፃ ሳለሁ፣ ምናቤ ገደብ አልነበረውም፤ ዓለምን ስለመለወጥም አልም ነበር፡፡ ዕድሜዬ እየገፋና ብልህ እየሆንኩ ስመጣ፣ ዓለም እንደማይለወጥ ተገነዘብኩ፡፡ እናም እይታዬን አጥብቤ፣ አገሬን ብቻ ለመለወጥ ወሰንኩኝ፡፡ እሱም ግን አልሆነም፡፡
የዕድሜዬ ማምሺያ ላይ፣ ሁሉን ትቼ ቤተሰቤን ለመለወጥ ተነሳሁ-የራሴን የቅርብ ሰዎች፡፡  ግን እሱም አልተሳካም፡፡
አሁን የሞት አልጋዬ ላይ ተንጋልዬ፣ ድንገት እንዲህ ስል አሰብኩ፡- መጀመሪያ ራሴን ለውጬ ቢሆን ኖሮ፣ በእኔ አርአያነት ቤተሰቤን ለመለወጥ እችል ነበር፡፡  ከእነሱ መነቃቃትና መበረታታት ተነስቼ ደግሞ፣ አገሬን መለወጥ እችል ነበር፤ ከዚያም ማን ያውቃል ዓለምን ሳይቀር ልለውጥ እችል ነበር፡፡
(ምንጭ፡- “Chicken soup for the soul” የተሰኘው መፅሃፍ )

Read 566 times