በአዳማ ከተማ የሚገኘውና በየወሩ ኪነጥበባዊ መሰናዶዎችን የሚያዘጋጀው የ”ግሪክ ኪነ ጥበባት” 21ኛ ምሽት የሆነው “ናፍቆት” የኪነ ጥበብ ምሽት በነገው ዕለት ከቀኑ 10፡00 በከተማዋ በሚገኘው ማፊ ሬስቶራንት አዳራሽ ውስጥ ይካሄዳል፡፡ በእለቱ ግጥም፣ ወግ፣ መነባንብ፣ ሙዚቃና ሌሎችም ኪነጥበባዊ መሰናዶዎች እንደሚቀርቡ የፕሮግራሙ አዘጋጅ ገጣሚ ተስፋ ብዙወርቅ ለአዲስ አድማስ ገልጿል፡፡ በእለቱ አንጋፋና ወጣት ደራሲያንና ገጣሚያን ሥራዎቻቸውን ለታዳምያኑ እንደሚያቀርቡም ለማወቅ ተችሏል፡፡
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና