በአዳማ ከተማ የተቋቋመው የሠዐሊያንና ቀራፂያን ማህበር ትናንት ከሰዓት በኋላ የመመሥረቻ ዝግጅቱን በቲታስ ኢንተርናሽናል ሆቴል እና በፖላስ ሆቴል አቀረበ፡፡ 35 አባላት ያሉት ማህበር ዝግጅት ማቅረቡን እስከ ነገ እንደሚቀጥል የማህበሩ ሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ ፎቶግራፈር ንጉሤ ተሾመ ለዝግጅት ክፍላችን ገልፀዋል፡፡ ማህበሩ በፎቶግራፍ፣ ሥዕልና ቅርፃ ቅርፅ 60 የአባላቱን ሥራዎች ለእይታ ያቀረበ ሲሆን ተመልካቾች ዝግጅቱን በነፃ እየታደሙት እንደሆነ ሃላፊው ገልፀው ትናንት በከተማዋ ፓላስ ሆቴል መናፈሻ በርካታ ባለሙያዎች የተሳተፉበት “ዝክረ መለስ” ሙዚቃዊ ድራማ መቅረቡንም አውስተዋል፡፡