ብሔራዊ ቤተ መዛግብትና ቤተ-መጻህፍት ኤጀንሲ (ወመዘክር) ከኢጋ ሚዲያና ኮሙኒኬሽን ጋር በመተባበር በሚያዘጋጁት ወርሃዊ መጽሐፍት ውይይት “ራስ” በተሰኘው የፍሬዘር መፅሐፍ ዙሪያ ዛሬ መጋቢት 17 ቀን 2014 ዓ.ም ከቀኑ 8፡00 ጀምሮ በወመዘክር አዳራሽ ውይይት ይካሄዳል።
ለውይይቱ የመነሻ ሀሳብ የሚያቀርቡት አቶ ዮናስ ታምሩ ሲሆኑ በውይይቱ ላይ በአካልም በዙምም መሳተፍ ለሚፈልጉ እንዲሳተፉ አዘጋጆቹ ግብዣ አቅርበዋል።
Saturday, 26 March 2022 10:42
በ”ራስ” መፅሀፍ ላይ ዛሬ ውይይት ይካሄዳል
Written by ናፍቆት ዩሴፍ
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና