በተለይ ለሕፃናት ኪነጥበባዊ ዝግጅቶች ቅድሚያ እንሰጣለን ያለችው የእናት ፋንታ፤ ለኪነጥበባዊ ዝግጅቶቹ ከሞሃ ለስላሳ መጠጥ ኢንዱስትሪ፣ ከቢጂአይ ኢትዮጵያ፣ ከአርቲስት ቴዎድሮስ መኮንን (ቴዲማክ)፣ ከአርቲስት ዘለቀ ገሠሠና ከሌሎችም ድጋፍ እንደተደረገላት ገልፃለች፡፡
በነገው የመጀመሪያ ዝግጅት አንጋፋው የማስታወቂያ ባለሙያ አቶ ውብሸት ወርቃለማሁ እና ገጣሚና ፀሐፌ ተውኔት አያልነህ ሙላቱ በክብር እንግድነት ሲገኙ ዲጄ ቤቢ፣ ዲጄ ሊ፣ ዲጄ ኤዲ፣ ዲጄ ጌት እና ዲጄ ናትሜሪ በሙዚቃ አቅራቢነት ይሳተፋሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡
ጋዜጠኛዋ በዚህ ምክንያት ከኢትዮጵያ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ድርጅት መልቀቅ እንደማትፈልግ ተናግራለች፡፡