Sunday, 18 September 2016 00:00

የፌስቡኩ መስራች፤ትራምፕ እንዲሸነፉ 20 ሚ. ዶላር መድቧል

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

 ከታዋቂው ማህበራዊ ድረገጽ ፌስቡክ መስራቾች አንዱ የሆነው ቢሊየነሩ ደስቲን ሞስኮቪትዝ፣ ዶናልድ ትራምፕ የአሜሪካ ቀጣዩ ፕሬዚዳንት ሆነው እንዳይመረጡ ለማድረግ የሚውል 20 ሚሊዮን ዶላር መመደቡን ፎርብስ መጽሄት ዘግቧል፡፡
ሞስኮቪትዝ እና ባለቤቱ ለዲሞክራት ፓርቲ ደጋፊ ቡድኖች 20 ሚሊዮን ዶላር በመለገስ፣ ቅስቀሳዎችን በዘመቻ መልክ እንዲያጧጡፉና ሄላሪ ክሊንተን ትራምፕን በመርታት፣ቀጣዩዋ የአሜሪካ ፕሬዚዳንት እንዲሆኑ ለማስቻል ድጋፍ እንደሚያደርጉ አስታውቀዋል፡፡ ዶናልድ ትራምፕ በምርጫ አሸንፈው የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ከሆኑ፣ አገሪቱ ወደ ውድቀት ማምራቷ አይቀርም፡፡ በአንጻሩ ሄላሪ ቢያሸንፉና ስልጣን ቢይዙ አገሪቱ ልእለ ሃያልነቷን አስጠብቃ ወደፊት ትጓዛለች፣ ስለዚህም ትራምፕ ወደ ዋይት ሃውስ የጀመሩትን ጉዞ ለማደናቀፍ፣እኔና ሚስቴ 20 ሚሊዮን ዶላር መድበናል ብሏል፤ሞስኮቪትዝ፡፡
ሞስኮቪትዝ ለትራምፕ ያለውን ተቃውሞ በይፋ ሲያስታውቅ ይህ የመጀመሪያ ጊዜው አይደለም ያለው ዘገባው፤ ባለፈው ሃምሌ ወር የትራምፕ መመረጥ የቴክኖሎጂ ፈጠራን አደጋ ላይ ይጥለዋል በሚል ፊርማቸውን ካሰፈሩ 145 ታዋቂ የቴክኖሎጂው ዘርፍ ባለሃብቶችና ተመራማሪዎች አንዱ  እንደነበርም አስታውሷል፡፡

Read 1200 times