Sunday, 04 September 2016 00:00

የሰሜን ኮርያ ምክትል ጠ/ ሚኒስትር በመንግስት መገደላቸው ተነገረ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

የሰሜን ኮርያ መንግስት፤ ከአገሪቱ ከፍተኛ ሚኒስትሮች አንዱ የነበሩትንና  በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የትምህርት ዘርፍ ሃላፊ ሆነው ሲሰሩ የቆዩትን ኪም ዩንግ ጂንን፣ባለፈው ወር ገድሏል ስትል ደቡብ ኮርያ መናገሯን ቢቢሲ ዘግቧል፡፡
ሚኒስትሩ ባለፈው የካቲት ወር ላይም ተገድለዋል ተብሎ ተወርቶ እንደነበር ያስታወሰው ዘገባው፤ይሄም ሆኖ ግን ከቀናት በኋላ በፓርቲው ምክር ቤት ስብሰባ ላይ ሲካፈሉ መታየታቸውን ጠቁሞ ይሄኛው የደቡብ ኮርያ መረጃም አጠራጣሪ ሊሆን እንደሚችል ገልጧል፡፡
ሰሜን ኮርያ ተገደሉ የተባሉትን ሚኒስትር በተመለከተ እስካሁን ያለቺው ነገር እንደሌለ የጠቆመው ዘገባው፣ የአገሪቱ መንግስት በቅርቡ የሚኒስትሩን ቦታ ተክቶ የሚሰራ ሌላ ሚኒስትር ከሾመ የመሞታቸው ነገር እርግጥ ሊሆን ይችላል መባሉን አመልክቷል፡፡
የሰሜን ኮርያ መንግስት ከዚህ ቀደምም ከፍተኛ ባለስልጣናቱንና ሚኒስትሮችን በድብቅና በይፋ በወሰዳቸው እርምጃዎች መግደሉን ዘገባው አስታውሷል፡፡

Read 1753 times