Monday, 29 August 2016 10:28

“ህዝብ በሚገባ ይናገር፤ እሱን እናዳምጠው” አቶ ኢየሱስወርቅ ዛፉ (የህብረት ኢንሹራንሽ የቦርድ ሊቀመንበር)

Written by 
Rate this item
(3 votes)

    ችግሩ በውይይት ይፈታ ሲባል የምሁራን የቃላት ስንጠቃና የፖለቲከኞች ውይይት እንዳይሆን ነው። ችግሩ በዚህ አንቀፅና በዚህ ንዑስ አንቀፅ በሚል ሳይሆን ዕድት ያለ አዕምሮ ይዞ፣ በመሰብሰብ ሁሉንም አሳትፎ፣ ምን እናድርግ? ይህቺ ሀገራች ነች፤ለሀገራችን ለህዝባችን የሚበጀው የቱ ነው? ብሎ እንደ አዲስ ማሰብ ያስፈልጋል ባይ ነኝ፡፡ ይሄ ደግሞ የምሁራኑና የፖለቲከኞች ብቻ መሆን የለበትም። የሁሉም የኢትዮጵያ ህዝብ ሀሳብ የሚወከልበት መድረክ መኖር አለበት፡፡ በተቻለ መጠን በተለይ በመንግስት በኩል በሰፊው ሊታሰብበት ይገባል።  የብልጣ ብልጦች ውይይት መሆን የለበትም። ለኢትዮጵያ ህዝብ እኛ ነን የምናውቅልህ ማለት አያስፈልግም፡፡ ሰፊው ህዝብ በሚገባ ይናገር፤እሱን እናዳምጠው፡፡ ይሄን ስናደርግ ደግሞ እየተቋሰልን እየተጋደልን መሆን የለበትም፡፡ በሁሉም በኩል ሰፊ ልብ ያስፈልጋል፡፡ በፅሞና ለመነጋገርም ጊዜ ያስፈልጋል፡፡ ታግሶ ነው መወያየት የሚያስፈልገው።

Read 6647 times