Sunday, 21 August 2016 00:00

የመን ባለፉት 16 ወራት የ14 ቢ. ዶላር ውድመት ገጥሟታል

Written by 
Rate this item
(2 votes)

ለአመታት በእርስ በርስ ጦርነት ስትታመስ የቆየችው የመን በመሰረተ ልማት አውታሮች ላይ በደረሰ ውድመትና በኢኮኖሚ ድቀት ሳቢያ በድምሩ 14 ቢሊዮን ዶላር ኪሳራ እንደደረሰባት ሮይተርስ ዘገበ፡፡
በየመን ላለፉት 16 ወራት በዘለቀው የእርስ በእርስ ጦርነት ከ6 ሺህ 500 በላይ ሰዎች ለህልፈተ ህይወት መዳረጋቸውንና ከ2.5 ሚሊዮን በላይ ዜጎችን ማፈናቀሉን የሚጠቁም ይፋ ያልሆነ ሪፖርት ማግኘቱን ያስታወቀው ሮይተርስ፤ከግማሽ በላይ የሚሆነው ህዝቧም የተመጣጠነ ምግብ እጥረት ተጠቂ መሆኑን ጠቁሟል፡፡ በአገሪቱ የእርስ በርስ ጦርነት ሳቢያ በርካታ መሰረተ ልማቶች መውደማቸውንና የኢኮኖሚ ድቀት መድረሱን የጠቆመው ዘገባው፤በአገሪቱ የሚገኙ 1 ሺህ 671 ትምህርት ቤቶች መውደማቸውንና ውድመቱ 269 ሚሊዮን ዶላር ይደርሳል ተብሎ እንደሚገመት አስረድቷል፡፡
የህክምና አገልግሎት ሲሰጡ ከነበሩ የአገሪቱ 3 ሺህ 652 ተቋማት መካከል 900 ያህሉ አገልግሎት መስጠት ማቆማቸውን የገለጸው ዘገባው፤በዚህም 2.6 ሚሊዮን የአገሪቱ ህጻናት ለበሽታ የመጋለጥ አደጋ ላይ መውደቃቸውን አስረድቷል፡፡

Read 964 times