ሚዩዚክ ሜይዴይ ከኢትዮጵስ ኮሌጅ ጋር በመተባበር ‹‹ዛሬም እንጉጎሮ›› በተሰኘው የፕሮፌሰር መስፍን ወ/ማሪያም የግጥም መፅሀፍ ላይ ነገ ከቀኑ 8፡00 ሰዓት ጀምሮ በብሄራዊ ቤተ- መፅሀፍትና ቤተ መዛግብት አዳራሽ ውይይት ይካሄዳል፡፡ ለውይይት የመነሻ ሀሳብ የሚያቀርቡት በደብረብርሀን ዩኒቨርሲቲ የስነ-ፅሁፍ መምህርና በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የፒ. ኤች.ዲ እጩ የሆኑት ደራሲ ታደለ ፈንታው እንደሆኑ የተገለፁ ሲሆን በውይይቱ ላይ የመሳተፍ ፍላጎት ያለው ሁሉ እንዲገኝ ሚዩዚክ ሜይዴይ ጋብዟል፡፡
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና