Saturday, 09 July 2016 10:07

የእንግሊዝ ጠቅላላ የአገር ውስጥ ምርት በ4.5 በመቶ ሊቀንስ ይችላል ተባለ

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

       የአለማቀፉ የገንዘብ ተቋም አይኤምኤፍ ማኔጂንግ ዳይሬክተር ክርስቲያን ላጋርድ፣ እንግሊዝ ከአውሮፓ ህብረት በመውጣቷ ሳቢያ በቀጣዩ አመት ጠቅላላ የአገር ውስጥ ምርቷ ላይ ከ1.5 በመቶ እስከ 4.5 በመቶ ያህል ቅናሽ ሊመዘገብ እንደሚችል አስታወቁ፡፡ ላጋርድ ባለፈው ሰኞ ከለሞንድ ጋዜጣ ጋር ባደረጉት ቃለመጠይቅ፤እንግሊዝ ባለፈው ሳምንት ባደረገቺው ህዝበ ውሳኔ ከህብረቱ አባልነቷ ለመውጣት መወሰኗ ከሌሎች አገራት ጋር በሚኖራት ቀጣይ የንግድ ግንኙነትና በአጠቃላይ ኢኮኖሚዋ ላይ ተጽዕኖ እንደሚኖረው ገልጸዋል፡፡
ውሳኔው አገሪቱ ከተቀሩት የአውሮፓ ህብረት አገራት ጋር ለሚኖራት የንግድ ግንኙነት አሳሳቢ ነው ያሉት ክርስቲያን ላጋርድ፤በእንግሊዝና በአውሮፓ ህብረት መካከል ውሳኔውን በተመለከተ የሚደረጉ ውይይቶች ምን ያህል ጊዜ ሊወስዱ እንደሚችሉ እርግጠኛ አለመሆናቸውን ጠቁመዋል፡፡
የአይኤምኤፍ ዋና ኢኮኖሚስት ሞሪስ ኦብስፊልድ በበኩላቸው፤የቀጣዩ አመት የእንግሊዝና የአለማቀፍ የኢኮኖሚ እድገት ትንበያዎች እንደ አዲስ ይከለሳሉ፤ውጤታቸውም አሉታዊ ይሆናል ሲሉ ባለፈው ሳምንት መናገራቸውም ተዘግቧል፡፡

Read 1296 times