Saturday, 02 July 2016 13:22

ሶማሊያ በዓለም የከፋ ያለመረጋጋት የታየባት አገር ተባለች

Written by 
Rate this item
(9 votes)

ኢትዮጵያ ከ178 የዓለም አገራት ባለመረጋጋት 24ኛ ደረጃን ይዛለች

የዓለማችንን አገራት ያለመረጋጋት አደጋ ደረጃ በየአመቱ ይፋ የሚያደርገውና ፈንድ ፎር ፒስ የተባለው ተቀማጭነቱ በአሜሪካ የሆነው የምርምር ተቋም ባለፈው ረቡዕ ባወጣው የ2016 አመታዊ ሪፖርት፤ ሶማሊያ ከፍተኛ ያለመረጋጋት ችግር የታየባት ቀዳሚዋ የአለማችን አገር መሆኗን አስታውቋል፡፡
የአገራትን አጠቃላይ ሁኔታ የሚያመለክቱ በሺዎች የሚቆጠሩ ሪፖርቶችንና ጽሁፎችን በመተንተን እንዲሁም ማህበራዊ፣ ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ሁኔታዎችን የሚያመላክቱ 10 ቁልፍ መስፈርቶችን መሰረት በማድረግ ደረጃ የሚሰጠው ተቋሙ፤ ለ12ኛ ጊዜ ባወጣውና 178 የአለማችን አገራትን ባካተተው ሪፖርቱ፣ ሶማሊያን በቀዳሚነት አስቀምጧታል፡፡ከሶማሊያ በመቀጠል ከፍተኛ ያለመረጋጋት ችግር ያለባት አገር ደቡብ ሱዳን እንደሆነች የጠቆመው ሪፖርቱ፤ መካከለኛው አፍሪካ ሪፐብሊክ፣ ሱዳን፣ የመን፣ ሶርያ፣ ቻድ፣ ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ፣ አፍጋኒስታንና ሃይቲ እስከ አስረኛ ያለውን ደረጃ እንደያዙ ገልጧል፡፡ኢትዮጵያን በ24ኛ ደረጃ ላይ ያስቀመጠው የዘንድሮው ፈንድ ፎር ፒስ ሪፖርት፤ አገሪቱ ባለፉት አራት አመታት የመረጋጋት ሁኔታዋ እየተሻሻለ  ቢመጣም፣ በአገሪቱ የቡድን ግጭቶችና የተማረ የሰው ሃይል ፍልሰት ከአምናው ጋር ሲነጻጸር ጭማሪ አሳይቷል ብሏል፡፡
ከአለማችን አገራት መካከል እጅግ ዘላቂ የሆነ መረጋጋት ያለባት አገር ፊንላንድ ናት ብሏል የተቋሙ ሪፖርት፡፡

Read 3304 times