በጋሻው መርሻ የተዘጋጀው በዕውቁ የቀዶ ጥገና ሃኪምና ፖለቲከኛ ፕሮፌሰር አስራት ወልደየስ ህይወት ላይ የሚያጠነጥነው “አንፀባራቂው ኮከብ፣ ፕ/ር አስራት ወልደየስ” የተሰኘ መፅሀፍ ሰሞኑን ለንባብ በቃ፡፡ ፀሐፊው ለመፅሀፉ የሚውሉ ግብአቶችን ለማሰባሰብ ሶስት ዓመት፣ መረጃዎቹን አጠናቅሮ ወደፅሁፍ ለመቀየር አንድ ዓመት ከሁለት ወራት እንደፈጀበት ለአዲስ አድማስ ገልጿል፡፡ ፕ/ሩ ከልጅነት ህይወታቸው ጀምሮ ስለትምህርታቸው፣ ስራቸው፣ በእስር ላይ በነበሩበት ጊዜ ስላደረጓቸው… ክርክሮች እስከ ዕድሜያቸው ፍፃሜ ድረስ ያለውን ህይወት በመፅሀፉ ለመዳሰስ ሞክሯል፡፡ ፀሐፊው ስለፕሮፌሰሩ ሙሉ ምስል ለማግኘት ወዳጆቻቸውን፣ የስራ ባልደረቦችን ቤተሰባቸውን ያነጋገረ ሲሆን በተለያዩ ጊዜያት የሰጧቸውን ቃለ ምልልሶች፤ የውጭና የአገር ውስጥ ሚዲያዎች ስለእሳቸው ያወጧቸውን ዘገባዎች መጠቀሙን ጠቁሟል፡፡ በ260 ገፆች የተቀነበበው መፅሀፉ፤ በ81 ብር ለገበያ ቀርቧል፡፡
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና