Saturday, 04 June 2016 12:50

ዙማ ለ4 ሚስቶቻቸው በገዟቸው 11 መኪናዎች ተከሰሱ

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

400 ሺህ ፓውንድ ከመንግስት በጀት ወጪ አድርገው ነው የገዙት
    የደቡብ አፍሪካው ፕሬዚዳንት ጃኮብ ዙማ፣ 400 ሺህ ፓውንድ የህዝብ ገንዘብ ወጪ በማድረግ ለአራት ሚስቶቻቸው 11 ዘመናዊ መኪኖችን ገዝተዋል በሚል የቀረበባቸውን ክስ የአገሪቱ ፍርድ ቤት ማጣራት መጀመሩ ተዘገበ፡፡ የህዝብ ገንዘብ ለግል ጥቅማቸው አውለዋል በሚል በተደጋጋሚ ሲከሰሱና ውሳኔ ሲተላለፍባቸው የከረሙት ዙማ፣ አሁን ደግሞ ይህን ያህል ገንዘብ አውጥተው ለሚስቶቻቸው የቅንጦት መኪና ገዝተዋል በሚል እንደተወነጀሉ የዘገበው ዘ ጋርዲያን፤መኪኖቹ ከአገሪቱ ፖሊስ በጀት ወጪ በተደረገ ገንዘብ መገዛታቸውን ጠቁሟል፡፡
የአገሪቱ የፖሊስ ሚኒስትር ንኮሲያንቲ ኔሊኮ ሰሞኑን መኪኖቹ መገዛታቸውን አምነው፣ ለፕሬዚዳንቱ ሚስቶች ደህንነት ሲባል ግዢው መፈጸሙ አግባብነት አለው ማለታቸውን ዘገባው አመልክቷል፡፡ ፍርድ ቤት ጉዳዩን እየተከታተለው እንደሚገኝም ተዘግቧል፡፡ ፕሬዚዳንቱ ለሚስቶቻቸው ገዟቸው ከተባሏቸው የቅንጦት መኪኖች ውስጥ አራት ሬንጅሮቨር ኤስዩቪ እና ሁለት ላንድሮቨር ዲስከቨሪ ኤስዩቪ የተባሉ እጅግ ዘመናዊ መኪኖች እንደሚገኙበትም ዘገባው አክሎ ገልጧል፡፡

Read 2090 times