Tuesday, 24 May 2016 08:31

አዲስ የኤችአይቪ ክትባት በደቡብ አፍሪካ ሊሞከር ነው

Written by 
Rate this item
(0 votes)

 እስካሁን ከተሞከሩት የተሻለ ውጤታማ ነው ተብሏል
   ከዚህ በፊት ከተሞከሩት የኤችአይቪ/ ኤድስ መከላከያ ክትባቶች ሁሉ የተሻለ ውጤት አስገኝቷል የተባለ አዲስ ክትባት በመጪው ህዳር ወር ላይ በደቡብ አፍሪካ ሊሞከር እንደሆነ ኤንቢሲ ኒውስ ዘገበ፡፡ የኤችአይቪ/ኤድስ ኢንፌክሽንን በአንድ ሶስተኛ ያህል የመከላከል አቅም አለው የተባለው ይህ ክትባት በቀጣይ ሊደረግ በታሰበው ሙከራ የበለጠ ውጤታማ ይሆናል ተብሎ እንደሚጠበቅ የጠቆመው ዘገባው፤ክትባቱ የሚሞከረው በ5ሺህ 400 ሰዎች ላይ እንደሚሆንም ገልጧል፡፡
ቫይረሱ በአለማቀፍ ደረጃ 35 ሚሊዮን ሰዎችን እንዳጠቃ የጠቆመው የኤንቢሲ ኒውስ ዘገባ፤በየአመቱ 1.2 ሚሊዮን ሰዎችን ለሞት እየዳረገ እንደሚገኝም አስረድቷል፡፡

Read 2168 times