Saturday, 09 April 2016 10:26

አፕል የዓለማችንን ምርጥ የቢሮ ህንጻ እየገነባ ነው

Written by 
Rate this item
(2 votes)

 ከ100 ቢሊዮን ብር በላይ መፍጀቱ ታውቋል
     ታዋቂው የሞባይልና የኮምፒውተር አምራች ኩባንያ አፕል፣ በ5 ቢሊዮን ዶላር ወጪ የዓለማችንን ምርጥ የቢሮ ህንጻ በካሊፎርኒያ እየገነባ መሆኑን ዘ ዴይሊ ሜይል ዘገበ፡፡ ግንባታው በመገባደድ ላይ የሚገኘው የአፕል ዋና መስሪያ ቤት የግንባታ ስምምነት የተፈጸመው ከ6 አመታት በፊት እንደነበር ያስታወሰው ዘገባው፣ ህንጻው በ260 ሺህ ስኩዌር ሜትር ቦታ ላይ ማረፉንና 13 ሺህ ያህል ሰራተኞችን መያዝ እንደሚችል ጠቁሟል፡፡
በክብ ቅርጽ ለተሰራውና የዙሪያ መጠኑ 1.6 ኪሎሜትር እርዝማኔ ላለው ለዚህ ግዙፍ ህንጻ የሚገጠሙት መስኮቶች በአለማችን በግዙፍነታቸው ቀዳሚውን ስፍራ እንደሚይዙ የተነገረ ሲሆን የግንባታው ወጪ 3 ቢሊዮን ዶላር ይሆናል ተብሎ ቢጀመርም ወጪው እየጨመረ መጥቶ 5 ቢሊዮን ዶላር መድረሱን ዘገባው ገልጧል፡፡
1 ሺህ መኪኖችን የማስተናገድ አቅም ያለው የመኪና ማቆሚያ ስፍራ በሚኖረው በዚህ ህንጻ ግቢ ውስጥ 7 ሺህ ያህል ዛፎች መተከላቸው የተገለጸ ሲሆን፣ ግንባታው በስምንት ወራት ጊዜ ውስጥ ሙሉ ለሙሉ ተጠናቅቆ አገልግሎት መስጠት እንደሚጀምር ይጠበቃል፡፡

Read 1800 times