Saturday, 27 February 2016 11:47

“ግጭቱ በሰላማዊ መንገድ እንዲፈታ እንጠይቃለን”

Written by 
Rate this item
(14 votes)

የኦፌኮ ሊቀመንበር ዶ/ር መረራ ጉዲና በኦሮሚያ በተከሰተው ግጭት፣መንግስት ሰሞኑን በሰጠው መግለጫና ተያያዥ ጉዳዮች ዙሪያ ተከታዩን አጭር የስልክ ቃለ-ምልልስ ከአዲስ አድማስ ጋዜጠኛ
አለማየሁ አንበሴ ጋር አድርገዋል፡፡

ቢሮአችሁ ሰሞኑን በፀጥታ ኃይሎች ቁጥጥር ስር ውሎ እንደነበር በተለያዩ ማህበራዊ ሚዲያዎች ተነግሯል -----
አዎ፡፡
ምን ነበር የተፈጠረው?
በቃ በእለቱ ሰው መግባትና መውጣት አይችልም ነበር ያሉን፡፡
ቢሮአችሁ ፍተሻ ተካሂዶበታል?
አልተካሄደም፡፡
የታሰረ ሰው አለ?
የለም፡፡
መቼ ነበር ይህ የሆነው?  
እሁድ፡፡
ከእሁድ በኋላስ ቢሮ መግባት ቻላችሁ ?
አዎ፡፡
በኦሮሚያ የተፈጠረውን ግጭትና የመንግስትን እርምጃ እንዴት ገመገማችሁት?
የህዝቡ እንቅስቃሴ አሁንም ቀጥሏል። መንግስትም እርምጃ መውሰዱን ቀጥሏል፡፡ እኛ ደግሞ ግጭቱ በሰላማዊ መንገድ እንዲፈታ እየጠየቅን ነው፡፡ ይሄ ነው ያለው ነገር፡፡
ፓርቲያችሁ ግጭቱ በሰላማዊ መንገድ እንዲፈታ ጥያቄ ያቀርባል?
አዎ! በፊትም ስናቀርብ ነበር፤አሁንም ግጭቱ በሰላማዊ መንገድ በውይይት እንዲፈታ ጥሪያችንን እናቀርባለን፡፡
መንግስት በኦሮሞ ህዝብ ስም የሚንቀሳቀሱ ፓርቲዎች በተከሰተው ግጭት ውስጥ እጃቸው እንዳለበት እየገለጸ ነው፡፡ ቀደም ሲል የእናንተ አባላትና አመራሮችም ታስረዋል፡፡ በተቃውሞው የኦፌኮ ሚና ምን ያህል ነው?
ህዝቡ ማንም ሳይቀሰቅሰው ከዳር እስከ ዳር ለመብቱ እየተንቀሳቀሰ ነው፡፡ በአንድ ፓርቲ ቅስቀሳ ብቻ አይነሳም፡፡ የህዝቡን ብሶት ራሱ ኦህዴድም ያውቀዋል እኮ፤እኛ የተለየ ነገር የለንም፡፡
መንግስት ችግሮቹን እንዴት መፍታት አለበት ይላሉ?
ኢህአዴግ ጉዳዩ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ቁጭ ብሎ መነጋገር አለበት፡፡
እንዴት ነው ህዝቡን ማረጋጋት የሚቻለው፣ ምን አይነት የፖለቲካ ድርድር መደረግ አለበት --- በሚሉት ዙሪያ መወያየት ያስፈልጋል፡፡ አሁን ብሄራዊ መግባባት፣ ብሄራዊ እርቀ ሰላም መፈጠር አለበት፤ ነገር ግን ኢህአዴግ በዚህ መንገድ እየሄደ አይደለም፡፡
ከሰሞኑ ግጭት ጋር በተያያዘ የታሰሩባችሁ አባላት አሉ?
እስርማ ሁሌም አለ፡፡ እስሩ አሁንም ቀጥሏል፡፡

Read 4573 times