Saturday, 06 February 2016 11:07

አቤል ተስፋዬ በጁኖ የሙዚቃ ሽልማት ዕጩነት እየመራ ነው

Written by 
Rate this item
(0 votes)

አቤል በ6፣ ጀስቲን ቢበር በ5 ዘርፎች ታጭተዋል

   ትውልደ ኢትዮጵያዊው የአር ኤንድ ቢ ሙዚቃ አቀንቃኝ አቤል ተስፋዬ ወይም ዘ ዊክንድ እና ታዋቂው ድምጻዊ ጀስቲን ቢበር የካናዳውያን የግራሚ ሽልማት ተብሎ በሚታወቀው የዘንድሮው የጁኖ የሙዚቃ ሽልማት በበርካታ ዘርፎች በመታጨት መሪነቱን መያዛቸውን ፎርብስ መጽሄት ዘገበ፡፡
የ25 አመቱ ኢትዮ-ካናዳዊ ድምጻዊ አቤል ተስፋዬ በዘንድሮው 45ኛው የጁኖ አመታዊ ሽልማት በስድስት ዘርፎች መታጨቱን የገለጸው ዘገባው፣ አምናም በአመቱ ምርጥ አርቲስት እና በአመቱ የአር ኤንድ ቢ ሶል ሪከርዲንግ ዘርፎች ተሸላሚ እንደነበር አስታውሷል፡፡
አቤል በዘንድሮው የጁኖ ሽልማት በዕጩነት ከቀረበባቸው ስድስት ዘርፎች፣ የአድናቂዎች ምርጫ፣ የአመቱ ምርጥ አልበምና የአመቱ ምርጥ የዘፈን ደራሲ... ይገኙባቸዋል ተብሏል፡፡
ጀስቲን ቢበርና ሌላው ታዋቂ ካናዳዊ ድምጻዊ ድሬክም በ2016 የጁኖ አለማቀፍ የሙዚቃ ሽልማት በአምስት ዘርፎች ለሽልማት መታጨታቸውን ያመለከተው ዘገባው፣ የሽልማት ስነስርዓቱ በመጪው ሚያዝያ ወር መጀመሪያ ላይ በካልጋሪ እንደሚካሄድም አክሎ ገልጿል፡፡

Read 835 times