የታዋቂው የሬጌ አቀንቃኝ የቦብ ማርሊ 71ኛ ዓመት የልደት በአል የዛሬ ሳምንት አርብና ቅዳሜ በተለያዩ የሙዚቃ ድግሶች በሻሸመኔ ከተማ እንደሚከበር አዘጋጆቹ ገልፀዋል፡፡
በሙዚቃ ድግሱ ላይ ሲድኒ ሰልማንና ራስ ጃኒን ጨምሮ ከዛምቢያ፣ ሴራሊዮን፣ አሜሪካና ሌሎች አገራት የተውጣጡ 14 አርቲስቶችና ዲጄዎች እንደሚሳተፉበት ታውቋል፡፡
የቦብ ማርሊን የልደት በዓል ምክንያት በማድረግ የሚቀርበው የሙዚቃ ድግስ ዋና ዓላማው፤ በስሙ የተሰየመውን ትምህርት ቤት ጨምሮ ሌሎች ፕሮጀክቶችን ለማገዝ የሚያስችል ገቢ ለማሳሰብ እንደሆነ ተገልጿል፡፡
በአሉን አለምአቀፍ ለማድረግ የተለያዩ ጥረቶችን እያደረግን ነው ያሉት አዘጋጆቹ፤ የሬጌ አድናቂው ማህበረሰብ በድግሱ ላይ እንዲታደም ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል፡፡
Published in
ጥበብ