ሚዩዚክ ሜይዴይ ኢትዮጵያ ከኢትዮጵስ ኮሌጅ ጋር በመተባበር፣ ነገ ከቀኑ 8፡00 ሰዓት ጀምሮ በብሄራዊ ቤተ - መፃህፍትና ቤተ - መዛግብት ኤጀንሲ አዳራሽ “የሀበሻ ጀብዱ” የተሰኘ መጽሐፍ ላይ ውይይት ያካሂዳል፡፡ በቼኮዝሎቫኪያ ተወላጁ ዶ/ር አዶልፍ ፓርላሳክ በተፃፈውና በተጫነ ጆብሬ መኮንን የተተረጎመው እንዲሁም በጣሊያን ወረራ ላይ በሚያተኩረው መፅሐፍ ላይ ለሚደረገው ውይይት የመነሻ ሀሳብ የሚያቀርቡት ጋዜጠኛና የታሪክ ተመራማሪው ታዲዮስ ታንቱ እንደሆኑ ታውቋል፡፡
Saturday, 23 January 2016 13:49
“የሀበሻ ጀብዱ” መፅሀፍ ላይ ነገ ውይይት ይካሄዳል
Written by ናፍቆት ዮሴፍ
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና