ታዋቂው ገጣሚና ደራሲ በዕውቀቱ ስዩም “ከአሜን ባሻገር” የተሰኘ አዲስ መጽሃፍ ያሳተመ ሲሆን በመጪው ሳምንት ገበያ ላይ ይውላል ተብሏል፡፡ “በመጽሐፌ ከጉዞ፣ ከኑሮና ከምርምር የቀሰመኩትን እውነታ ለማካፈል ጥረት አድርጌያለሁ፡ ፡” ብሏል፤ በዕውቀቱ በፌስቡኩ ላይ ባሰፈረው ጽሁፍ፡፡በ2004 ዓ.ም በለንደን ኦሎምፒክ ከዓለም ዕውቅ ገጣሚያን ጋር የግጥም ሥራውን ያቀረበው በዕውቀቱ፤በአሁኑ ወቅት በአሜሪካ ሃዋርድ ዩኒቨርሲቲ በትምህርትና ምርምር ላይ ይገኛል፡፡
ከዚህ ቀደም ደራሲው “ነዋሪ አልባ ጎጆዎች”፣ “በራሪ ቅጠሎች;፣ “እንቅልፍና ዕድሜ”፣ “መግባትና መውጣት” የተሰኙ የሥነጽሁፍ ሥራዎቹን ለንባብ አብቅቷል፡፡
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና