አንድ ሰውዬ በኒውዮርክ ሴንትራል ፓርክ በእግሩ
እየተጓዘ ሳለ አንዲት ህፃን በትልቅ ውሻ ስትነከስ
ይመለከታል፡፡ በሩጫ ይሄድና አንዳች ከሚያህለው
ውሻ ጋር ትግል ይጀምራል። በመጨረሻም ውሻውን
በመግደል የህፃኗን ህይወት ይታደጋል፡፡ ትእይንቱን
ሲመለከት የነበረ ፖሊስ ወደ ሰውየው በመጠጋት፤
“ጀግና ነህ፤ ይሄ ተግባርህ ነገ በሁሉም ጋዜጦች ላይ
ተዘግቦ ታነበዋለህ” ይለዋል፡፡ ፖሊሱ በዚህ ብቻ
አልበቃውም፡፡ የዜናው ርእስ ምን ሊሆን እንደሚችል
ሁሉ ይተነብይለት ጀመር፡፡
“ጀግናው የኒውዮርክ ነዋሪ የህፃኗን ህይወት ታደገ”
“እኔ ግን የኒውዮርክ ነዋሪ አይደለሁም” አለ
ሰውየው፡፡
እንግዲያውስ የጠዋት ጋዜጦች እንዲህ ብለው
ያወጡታል፡-
“ጀግናው አሜሪካዊ የህፃኗን ህይወት ታደገ”
“እኔ እኮ አሜሪካዊ አይደለሁም” አለ ሰውየው
በድጋሚ፡፡
“ታዲያ ምንድን ነህ?” ጠየቀ ፖሊሱ፡፡
“የፓኪስታን ተወላጅ ነኝ”
* * *
በነገታው የወጡት ጋዜጦች፤ “ፅንፈኛው
ሰላማዊውን የአሜሪካ ውሻ ገደለ” ብለው ዘገቡ፡፡
Published in
ጥበብ