Saturday, 19 December 2015 10:49

“ድፍርስ” መፅሐፍ ለንባብ በቃ

Written by 
Rate this item
(2 votes)

የአዕምሮ ህክምና ስፔሻሊስትና በሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ ህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ የአዕምሮ ህክምና ትምህርት ክፍል ረዳት ፕሮፌሰር በሆኑት ዶ/ር ሞገስ አየሁ የተፃፈውና በአዕምሮ ህመምና ህሙማን ህይወት ላይ ትኩረቱን ያደረገው “ድፍርስ” የተሰኘ መጽሐፍ ሰሞኑን ለንባብ በቅቷል፡፡
በ18 ክፍሎች የተዘጋጀው ይኸው መጽሐፍ፤ ስለ አንጐል መታወክና መንስኤዎቹ፣ ስለ አዕምሮ ህመም ምንነት፣ አዋቂና ህፃናት ላይ ስለሚከሰት የአዕምሮ ህመም፣ ስለ ኦቲዝምና ሌሎች ከአዕምሮ ጋር የተያያዙ ጉዳዮች ጥልቅ ትንታኔን ይዟል፡፡ በመጽሐፉ ሽፋን ላይ አስተያየቱን ያሰፈረው ደራሲ እንዳለጌታ ከበደ፤ “ዶክተሩ የፃፉት ይህ መጽሐፍ የሚጠቅመው ለአዕምሮ ህሙማንና ለአሳታሚዎች ብቻ ሳይሆን በዘርፉ ኪናዊ ስራ ለሚሰሩ ገጣሚያን፣ ልቦለድ ደራሲያንና ፊልምና ቴአትር ለሚሰሩም የጥበብ ሰዎች ግብአት የሚሆን ነው” ብሏል፡፡ በ184 ገጾች የተሰናዳው መጽሐፉ፤ ለአገር ውስጥ በ75 ብር፣ ለውጭ አገራት በ20 ዶላር ይሸጣል። 

Read 1282 times Last modified on Saturday, 19 December 2015 11:00