አንጋፋዋ የጥበብ ባለሙያ አልጋነሽ ታሪኩ ለ50 ዓመታት የሰራቻቸው ዘመን ተሻጋሪ ስራዎቿ የተዘከሩበት የኪነጥበብ ፕሮግራም ከትላንት በስቲያ ጠዋት በኢትዮጵያ ብሔራዊ የባህል ማዕከል ተከናወነ፡፡
በእለቱ የአርቲስቷ ስራዎች፣ የጥበብ አጀማመሯ፣ በኪነጥበቡ ያሳለፈቻቸው ፈተናዎችና ስኬቶቿ የተወሱ ሲሆን የተለያዩ የኪነ - ጥበብ ዝግጅቶችም ቀርበዋል፡፡
በዚህ ፕሮግራም ላይ የአርቲስቷ የሙያ ጓደኞች፣ ወዳጅ ዘመዶች፣ የኪነጥበብ አፍቃሪያን፣ የባህልና ቱሪዝም ተወካዮችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ታድመው ነበር፡፡
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና